Friday, 13 September 2013 12:35

ሳያልፍብን ውዴ...

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ዘመን ሳይለወጥ እቴ ውዴ ሆይ
መግደርደር ተይና አንዴ እንተያይ!
ዝናቡን ዘንግተሽ፤ ጳጉሜን ግን አስታውሰሽ
ዣንጥላ ሳትይዢ በታክሲም ሳትመጪ
እንጠመቅ ፍቅር ከዝናብ ጋር ውጪ፡፡
ወደ አውላላ ሜዳ ተሸክሜሽ ልክነፍ
ያንቺ ጉልበት እስኪያልቅ
የኔ እስኪንጠፈጠፍ፤
ወድቀን እንጫወት
ፍቅር ለጭቃ አይሰንፍ!
ከዚያም እንተኛ ትራስ ሆኖሽ ክንዴ
የጭቃ ላይ ፍቅር ውብም አደል እንዴ?
እንደተጋደምን እንደተዋሃድን
ለፍቅራችን ማህተም ትሆንልን ዘንዳ፤
ፍቀጅላት ውዴ - መስከረም አንድ ሲል
ከናፍራችን ላይ
አደይዋ ትፈንዳ!
ለዑል ብርሃኑ
ነሐሴ 26/97

Read 5272 times