Monday, 16 September 2013 07:35

ዜድ ቲ ኢ ለ70 ቤተሰቦች የአዲስ ዓመት ድጋፍ አበረከተ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የአዲስ ዓመትን በዓል ምክንያት በማድረግ ዜቲኢ ኮርፖሬሽን በአዲስ አበባ የተለያዩ ክፍለከተሞች ለሚገኙ 70 ችግረኛ ቤተሰቦች የአዲስ ዓመት ድጋፍ አበረከተ፡፡
ባለፈው ማክሰኞ በአዲስ ዓመት ዋዜማ ዜድቲኤ ባደረገው ድጋፍ ለእያንዳንዱ ቤተሰብ አንድ እሽግ ደብተርና አምስት ኪሎ ስጋ የሰጠ ሲሆን በዕለቱ ህፃናትና ቤተሰቦች በኮርፖሬሽኑ ድጋፍ መደሰታቸውን ተናግረዋል፡፡
የዜቲኢ ሥራ አስኪያጅ ሚ/ር ሃን ኤችአር ድጋፉን አስመልክተው ሲናገሩ፤ “ዜቲኢ በመሰረተ ልማት አቅርቦት ስራ ላይ የተሰማራ ኩባንያ ብቻ ሳይሆን፤ ከማህበረሰቡ ጋር በጥብቅ የተቆራኘና የህዝቦችን አቅም በማጐልበት የሚያምን ነው” በማለት ኩባንያው ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ በደስታና በብልጽግና የተሞላ አዲስ ዓመት እንደሚመኝ ገልፀዋል ያሉት የጉለሌ ክፍለከተማ የሰራተኛ ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ መሰረት መንገሻ በበኩላቸው፤ “የዜቲኢን ድጋፍ በደስታ የምንቀበለው ነው፡፡” “ድጋፉ ኮርፖሬሽኑ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ያለውን ቅርርብና የህዝቡን አቅም በማጐልበት ረገድ የድርሻውን ለማበርከት ያለውን በጐ ፈቃድ ያሳያል።” ብለዋል - የዜቲኢ ድጋፍ ወደፊትም እንደሚቀጥል ያላቸውን ምኞት በመግለጽ፡፡

Read 1257 times