Monday, 16 September 2013 07:41

የኢትዮጵያ ጤና አጠባበቅ ማኅበር በ100 ሚ.ብር ሕንፃ ሊገነባ ነው

Written by  መንግሥቱ አበበ
Rate this item
(2 votes)

የኢትዮጵያ ጤና አጠባበቅ ማኅበር በ100 ሚሊዮን ብር ለሚያስገነባው የዋና መ/ቤት ሕንፃ የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱ ዛሬ የመሠረት ድንጋይ ያኖራሉ፡፡
ቀበና ሼል በመባል በሚጠራው አካባቢ የሚሠራው ሕንፃ 2 ምድር ቤትና ሰባት ፎቅ ሲኖሩት ማኅበሩ በሊዝ በገዛው 885 ካ.ሜ ስፍራ እንደሚያርፍ ታውቋል፡፡
የሕንፃው ዲዛይን በኤም ኤች ኢንጂነሪንግ የተሠራ ሲሆን የሕንፃው ግንባታ ሲጠናቀቅ የማኀበሩ ዋና ጽ/ቤት ሆኖ ከማገልገሉም በላይ፣ ምርጥ የጤና አጠባበቅ ማስተማሪያ፣ ማሠልጠኛ፣ የምርምር ማዕከል፣ የኅትመት ክፍሎችና፣ ቋሚ የስብሰባ አዳራሽ እንደሚኖረው ለማወቅ ተችሏል፡፡
በሥነ ሥርዓቱ ላይ ከክብር እንግዳው በተጨማሪ የኢትዮጵያ ጤና አጠባበቅ ማኅበር የበላይ ጠባቂ፣ የዓለም አቀፍ ድርጅትና ኤጀንሲ ተወካዮች፣ የዲፕሎማቲክ አባላት፣ የልማት አጋሮችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እንደሚገኙ ታውቋል፡፡

Read 10455 times