Monday, 16 September 2013 07:43

በአራቱ የሙስና ተጠርጣሪዎች ላይ የመጨረሻ የምርመራ ጊዜ ተፈቀደ

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(2 votes)

በከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩትና የምርመራ ሂደታቸው ባለመጠናቀቁ ጉዳያቸው ወደ ምርመራ መዝገብ የተመለሰው እነ አቶ ምህረትአብ አብርሃ፣ በእግዚአብሔር አለበል፣ ተክለአብ ዘርአብሩክ እና ፍፁም ገ/መድህን ላይ በትናንትናው እለት በዋለው ችሎት ለመጨረሻ ጊዜ ተብሎ የ7 ቀን የምርመራ ጊዜ ለ3ኛ ጊዜ ተፈቀደ፡፡
የፌደራሉ የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን መርማሪ ቡድን ቀደም ሲል በነበረው ችሎት በተሰጠው የ8 ቀን የምርመራ ጊዜ በአብዛኛው የኦዲት ስራ መጠናቀቁን በመግለጽ፣ ቀሪ የአንድ ኩባንያ የኦዲት ስራ ባለመጠናቀቁ ተጨማሪ የ14 ቀን ጊዜ እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡
ተጠርጣሪዎች በበኩላቸው፤ በምርመራ ሰበብ ያለ አግባብ እየተጉላሉ መሆኑንና ሌሎች የየግል ምክንያታቸውን በማቅረብ የምርመራ ጊዜ የሚፈቀድ ከሆነ ጉዳያቸውን በዋስ ሆነው እንዲከታተሉ ጠይቀዋል፡፡ የግራ ቀኙን የቃል ክርክር ሲያዳምጥ የቆየው ፍ/ቤቱም፤ መርማሪ ቡድኑ ከጠየቀው የ14 ቀን ውስጥ 7 ቀን ብቻ በመፍቀድ ለመጨረሻ ጊዜ በሚል መዝገቡን ለመስከረም 10 ቀጥሯል፡፡

Read 11614 times