Monday, 16 September 2013 08:17

‹‹ፍቅርና ተስፋ›› እና ‹‹አጋምና ቁልቋል›› ልቦለዶች ለንባብ በቁ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበርና በብርሐንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት በጋራ አስተዳደር ተዟዟሪ ሂሳብ ለህትመት የበቃው ‹‹ፍቅርና ተስፋ›› የተሰኘው የተሾመ ወልደሥላሴ ረጅም ልቦለድ፣ ሰሞኑን ለገበያ ቀረበ፡፡ ልቦለዱ፣ ከ1960ዎቹ ጀምሮ የነበረውን የሀገሪቱን ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ባህላዊና ሥነልቦናዊ ጣጣዎችን በመተረክ፣ ለገነገኑ ሀገራዊ ችግሮች መፍትሔ የሚጠቁም አስተሳሰቦች የተንጸባረቁበት እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ መጽሐፉ፣ 380 ገጾች ያሉት ሲሆን፣ ዋጋው 55 ብር እንደሆነ ታውቋል፡፡
በኤርሚያስ መኮንን የተጻፈው፣ 178 ገጾች ያሉት ‹‹አጋምና ቁልቋል›› ረጅም ልቦለድም ባለፈው ሳምንት ለንባብ በቅቷል፡፡ መጽሐፉ በሽፋኑ ላይ፣ ‹‹በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ ልብ-ወለድ›› ስለመሆኑና ‹‹ የትዳር ተጣማሪዎች በአሜሪካ የሚያጋጥማቸውን ችግርም ቁልጭ አድርጎ ያሳያል›› ሲል ጠቁሟል፡፡ በውሥጥ ገጹ ላይ ደግሞ፣ ባልተለመደ ሁኔታ ደራሲው በ1988 ዓ.ም. አድራሻው ስለጠፋበት ወንድሙ፣ ያፋልጉኝ ማስታወቂያ ያወጣ ሲሆን፣ በ39 ብር ለገበያ መቅረቡም ታውቋል፡፡

Read 3176 times