Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Saturday, 26 November 2011 08:48

“ትዋይላይት” የዓለም ወጣቶችን ትኩረት ስቧል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

“ዘ ትዋይላይት ሳጋ፡ ብሬኪንግ ዳውን” የተሰኘው ፊልም የመጀመርያ ክፍል ሰሞኑን ለዕይታ የቀረበ ሲሆን በመላው ዓለም የወጣቶችን ትኩረት እንደሳበ ተዘገበ፡፡ በቫምፓየሮች አኗኗር እና የፍቅር ጉዳዮች የሚያጠነጥን ጭብጥ ያለው ፊልሙ፤ በመላው ዓለም እድሜያቸው ከ18 እስከ 30 በሚደርሱ ወጣቶች ከፍተኛ ትኩረት ማግኘቱ ገበያውን አሟሙቆለታል፡፡ በሰሜን አሜሪካ ብቻ በሦስት ቀናት 142.8 ሚሊዮን ዶላር ያስገኘው ፊልሙ፤ በምረቃው ሰሞን በቦክስ ኦፊስ ታሪክ ከፍተኛውን ገቢ በማስመዝገብ 5ኛ ደረጃ ተሰጥቶታል፡፡

ሰሞኑን በመላው ዓለም በጠቅላላ 283.5 ሚሊዮን ዶላር ገቢ እንዳስገኘ ታውቋል፡፡ በ110 ሚሊዮን ዶላር በጀት በ”ሰሚት ኢንተርቴይመንት” የተሰራው የዚህ ፊልም ሁለተኛ ክፍል ከዓመት በኋላ ለተመልካች ይቀርባል፡፡ በስቴፌን ሜየር የቫምፓየር መፅሃፍ ላይ ተመስርተው የተሰሩት የመጀመርያ ሶስት ክፍል ፊልሞች በዓለም ዙርያ 1.8 ቢሊዮን ዶላር አስገብተዋል፡፡ የ”ትዋይላይት” ገበያ በአራት ፊልሞችና ሶስት ተከታታይ መፅሃፎች ሽያጭ ብቻ አያበቃም፡፡ ከፊልሙ ጋር የተያያዙ የአልባሳት፤ የተለያዩ ቁሳቁሶችና ምርቶች ገበያም ደርቷል፡፡ የፊልሙ መሪ ተዋናዮች ሮበርት ፓቲርሰንና ክርስትያን ስተዋርት በመጨረሻዎቹ ሁለት ፊልሞች እያንዳንዳቸው 25 ሚሊዮን ዶላር ተከፍሏቸዋል፡፡ የመፅሃፍቱ ደራሲ ስቴፈን ማዬር ደግሞ ባለፈው ዓመት ገቢዋ 40 ሚሊዮን ዶላር መድረሱን ያመለከተው ፎርብስ መፅሄት፣ ሶስቱ የ”ትዋይላይት” መፅሃፍት በዓለም ዙርያ ሽያጫቸው ከ100 ሚሊዮን ዶላር መብለጡን ዘግቧል፡፡

 

Read 3031 times Last modified on Saturday, 26 November 2011 08:52