Saturday, 19 October 2013 12:15

የእናቶች ሞት በኢትዮጵያ በየአመቱ 4.9 % ያህል እየቀነሰ ነው

Written by  ፀሐይ ተፈረደኝ (ከኢሶግ)
Rate this item
(1 Vote)

               እ.ኤ.አ 2013 ዓ/ም ወደ ማለቂያው እየተዳረሰ ነው፡፡ የዛሬ አስራ ሶስት አመት ማለትም እ.ኤ.አ በ2000/ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ሀገራትን አስተባብሮ አለም አቀፍ የልማት ግቦችን መንደፉ ይታወሳል፡፡ 189/ የተባበሩት መንግስታት አባል ሀገራት በጋራ ወደ ስምንት የሚደርሱ የልማት ግቦችን ከነበሩበት ደረጃ እስከ 2015/ዓ/ም መሻሻል እንዲያሳዩ ሲታቀድ በዚ ህም ወደ 23/ የሚደርሱ አለም አቀፍ ድርጅቶች ግቡ እንዲሳካ ድጋፍ ለማድረግ ቃል የገቡ በት መድረክ ይታወሳል፡፡ ከእነዚህ ስምንት የልማት ግቦች ውስጥ የተወሰኑት ከጤና ጋር የተ ያያዙ ናቸው፡፡ በቅርቡ በተሰማው ዜና የልማት ግቦቹን ከማሳካት አንጻር በተለይም በአፍሪካ ወደ አምስት ሀገሮች በአብዛኛው የተሳካላቸው መሆኑ እና ኢትዮጵያ እንዲያውም ቀዳሚውን ስፍራ እንደያዘች ተገልጾአል፡፡ በኢትዮጵያ በተለይም ከሕጻናት ሞት ጋር የተያያ ዘው የልማት ግብ የተሳካ መሆኑ ቀደም ብሎ ተገልጾአል፡፡ ነገር ግን ከእናቶች ጤና ጋር በተያዘ የታለመወ ግብ እስከአሁን ድረስ ከተጠበቀበት ያልደረሰ በመሆኑ ወደፊት በተወሰነለት ጊዜ ከግቡ መድረስ ይችላልን? ከሚል ለሚሰነዘሩ ጥያቄዎች በኢፊድሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሚኒስትር ዶ/ር አሚር አማን ለጋዜጠኞች ማብራሪያ ቸውን ሰጥተዋል፡፡
                                              -----///------
ጥ/ የምእተ አመቱ የልማት ግብ ከጤና አኩዋያ ከምን ደረጃ ላይ ይገኛል ?
መ/ ከምእተ አመቱ የልማት ግቦች መካከል ቁጥር 4 ፣5 እና 6 / በቀጥታ ከጤና ጋር የተገናኙ ናቸው፡፡ ከእነዚህ ውስጥ በተራ ቁጥር 4/ የተመዘገበው የህጻናትን ሞት መቀነስ የሚባለውን በተባበሩት መንግስታት እንደተረጋገጠው ኢትዮጵያ በ2012ዓ/ም አሳክታለች፡፡ በ6ኛው ተራ ቁጥር የተመዘገበው የልማት ግብ ተላላፊ በሽታዎችን ፣ ሳምባን ፣ወባንና ኤችአይቪን መቀነስ ሲሆን ይህንንም ኢትዮጵያ በልማት ግቡ እቅድ መሰረት ካሳኩት አገራት መካከል ተመድባለች፡፡ ነገር ግን ትልቁ ችግር በተራ ቁጥር 5/ የተመዘገበው ከእናቶች ጤና ጋር የተያያዘው የልማት ግብ ምንም እንኩዋን እስከአሁንም ብዙ የተሰሩ ስራዎች ቢኖሩም ከተፈለገው ደረጃ ግን አልተደረሰም፡፡ ስለዚህም ክፍተት ስለሚታይ ገና ብዙ መስራት እንደሚጠበቅብን ግልጽ ነው፡፡
ጥ/ የምእተ አመቱን ቁጥር 5 /የልማት ግብ ለማሳካት በኢፊድሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስር ምን በመደረግ ላይ ነው?
መ/ የእናቶች ሞት ከሚመጣባቸው ምክንያቶች መካከል ሶስቱ መዘግየቶች የሚባሉት ትልቅ ችግር እንደሆኑ ይታወቃል፡፡
የመጀመሪያው መዘግየት እናቶች ከመውለዳቸውም በፊት ሆነ ከወለዱ በሁዋላ ወደ ጤና ተቋም ሄደው ከሕክምና ባለሙያ ጋር ምክር አለማድረጋቸው እና በወሊድ ጊዜ በጤና ተቋም ሄደው አለመው ለዳቸው ነው፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ የቤተሰብ የልማድ፣ የባህል የመሳሰለው የአመለካከት ችግር ወደጤና ተቋም ሄደው እንዳይወልዱ ማድረግ አንዱ ተጠቃሽ ችግር ነው፡፡ ይህንን ችግር ለመፍታት በጤና ጥበቃ ሚኒስር የጤና የልማት ሰራዊት የሚባል በአገር ደረጃ ኃይል የተደራጀ ሲሆን አንድ ለአምስት በሆነ አሰራር እናቶችን፣ ቤተሰቡን የሚመለ ከተውን ሁሉ በሚያዳርስ መልክ እንዲሁም የልማት ቡድን በማዋቀር ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ነው፡፡ የዚህ ስራ ዋና አላማው ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል በተለይም እናቶችን በማነቃቃት የአመለካከትን ችግር ለመለወጥ ነው፡፡ ይህም በተግባር እየተተረጎመ ነው፡፡
ሁለተኛው መዘግየት የሚባለው እናቶች ወደ ሆስፒታል መሄድ እየፈለጉ በትራንስፖርት ችግር ምክንያት መቅረታቸው ነው፡፡ የጤና ጥበቃ ሚኒስር ይህንን ችግር ለመፍታት በሁለት መንገድ እየተከታተለው ነው፡፡
እናቶችን ወደ ጤና ተቋም ለማድረስ እስከዋና መንገድ ድረስ ማለትም መኪና ሊገባበት እስከሚችለው መንገድ ድረስ ባህላዊ አምቡላንሶችን በአካባቢው ቁሳቁስ እንዲዘጋጁ በማድረግ በአካባቢው በሚኖሩ ወጣቶች አማካኝነት በማጉዋጉዋዝ ላይ ስንሆን በዚህም ትልቅ ለውጥ እየታየ ነው፡፡
እናቶች በባህላዊ አምቡላንስ አማካኝነት ወደ ዋና መንገድ ከደረሱ በሁዋላ ደግሞ አምቡላንስ በማቅረብ ወደጤና ተቋም እንዲደርሱ እየተደረገ ነው፡፡ ጤና ጥበቃ ሚኒስር በወረዳ ደረጃ አንድ አምቡላንስ ... ባጠቃላይም ወደ ስምንት መቶ አምቡላንሶችን አሰማርቶ አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው። የአንቡላንሶቹን አቅርቦት በተለይም ሰፋፊ ወረዳዎች ላይ ቁጥራ ቸውን ለመጨመር እንዲቻል አሁንም ወደ አራት መቶ አምቡላንሶች የተ ዘጋጁ ሲሆን በቅርቡ ለተገልጋዩ ይቀርባሉ። ስለዚህ ሁለተኛውን መዘግየት በዚህ መንገድ ለመቅረፍ ስራ በመሰራት ላይ ነው፡፡
ሶስተኛው መዘግየት የሚባለው እናቶች ጤና ተቋም ከደረሱ በሁዋላ በጤና ተቋም አማካኝነት የሚደርሱባቸው ችግሮች ናቸው፡፡ ይኼውም የሚገለጸው ፡-
የጤና ተቋማቱ ለእናቶች በቅርበት አለመኖራቸው፣
እናቶች የሚፈልጉትን አገልግሎት በተገቢው ሁኔታ አለማቅረብ፣
የሚሉት በሶስተኛው መዘግየት የሚጠቀሱ ናቸው። ይህንንም ለመቅረፍ በኢትዮጵያ በመጀመሪያ ደረጃ ጤና አገልግሎት ከ3200 ሶስት ሺህ ሁለት መቶ በላይ ጤና ጣቢያ ዎች እና ከ 17000 አስራ ሰባት ሺህ በላይ ጤና ኬላዎች እንዲሁም 126 አንድ መቶ ሀያ ስድስት የገጠር ሆስፒታል በስራላይ ያሉ ሲሆን በተጨማሪም 150 አንድ መቶ ሀምሳ በዚህ አመት ወደስራ ይገባሉ፡፡ ስለዚህ አጠቃላይ ያለውን ሽፋን ከ95% ማድረስ ተችሎአል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የተለያዩ የህክምና መሳሪያዎችን በመድሀኒትና አቅርቦት ፈንድ ተቋም ለማቅረብ ተችሎአል፡፡
ጥ/ የእናቶችን ሞት ለመቀነስ በከፍተኛ ሁኔታ መሰራት ይገባዋል የሚባለው የትኛው ነው?
መ/ የእናቶችን ሞት ለመቀነስ በከፍተኛ ሁኔታ መሰራት አለበት የሚባለው የጤና ባለሙያዎችን በሚመለከት ነው፡፡ የጤና ባለሙያዎች ሲባልም ሐኪሞች ፣ነርሶች ፣ሚድ ዋይፎች ፣ኼልዝ ኦፊሰሮች ፣የጽንስና ማህጸን ሕክምና እስፔሻሊስቶች ያስፈልጋሉ፡፡ ይህንን የባለሙያ እጥረት ለመቅረፍ በሕክምናው ዘርፍ የተወሰኑ አመታትን ከሰሩ በሁዋላ ለማስተማር ከፍተኛ ስራ እየተሰራ ነው፡፡ ዩኒቨርሲቲዎችም የቅበላ አቅማቸውን በመጨመር ትምህርቱን በማስተማር ላይ በመሆናቸው አበረታች ሁኔታ እየታየ ነው፡፡ ነገር ግን አንድን ጠቅላላ ሐኪም የጽንስና ማህጸን ሐኪም ለማድረግ አራት አመት ይፈጃል፡፡

ስለሆነም ለምእተአመቱ የልማት ግብ ውጤታማነት ለመድረስ አዳጋች ስለሚሆን የጤና ጥበቃ ሚኒስር እንደ ኢሶግ ካሉ አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር ባለሙያዎች አቅማቸውን እንዲያደረጁ በማድረግ ላይ ነው፡፡ በዚህ አሰራርም የጤና መኮንኖችን ሶስት አመት በማሰልጠን በአፋጣኝ የጽንስና ማህጸን ሕክምና ስራ ላይ እንዲሰማሩ ለማድረግ ገጠር ላሉ ጤና ተቋማት ለእያንዳንዱ ሁለት ሁለት ለማዳረስ በማሰብ አንድሺህ ባለሙ ያዎችን ለማሰልጠን ሁኔታዎች እየተመቻቹ ነው፡፡ ከእነዚህ ውስጥ ሁለት መቶ የሚሆ ኑት ስልጠናቸውን ጨርሰው ወደ የሆስፒታሉ የተመደቡ ሲሆን ከዚያም በላይ ይጠበ ቃል፡፡ አንድ የጤና ባለሙያ ቀዶ ሕክምና በሚያካሂድበት ጊዜ ስራውን ብቻውን ስለማይሰራው አዋላጅ ነርሶች እንዲሁም ሰመመን ሰጪዎችም አብ ረው ስልጠናውን እየወሰዱ ነው፡፡ ስለዚህ ሙያው እጅ ለእጅ በመያያዝ መልክ ከግንዛቤ ማስጨበጥ እስከጤና ባለሙያ ማፍራት ድረስ በመሰራት ላይ በመሆኑ የእና ቶችን ሞት ለመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ይታመናል፡፡
የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ይርጉ ገ/ሕይወት በምእተ አመቱ የልማት ግብ በተለይም በተራ ቁጥር 5/የተመዘገበው የእናቶች ሞትን መቀነስ በሚመለከት በሰጡት አስተያየት፡-
“… በእርግጥ ብዙ ስራዎች እየተሰሩ ነው፡፡ ነገር ግን የሚሰሩት ስራዎች በአፋጣኝ ውጤት የሚገኝባቸው ላይሆኑ ይችላሉ፡፡ ነገር ግን የተሰሩ ስራዎች ነገ ተነገወዲያ ጥሩ ውጤት እንደሚያሳዩ እሙን ነው፡፡ የእናቶችን ሞት ከሶስቱ መዘግየቶች ጋር ብቻ አያ ያዘን የምእተ አመቱን ግብ አልተሳካም ብለን መደምደም የለብንም፡፡ ምክንያቱም እናቶ ችን ከማዳን አንጻር ሌሎች ብዙ የሚጠቀሱ ስራዎች ተሰርተዋል፡፡ ኤችአይቪ ኤይድስ ለእናቶች ሞት ቀጥተኛ ባልሆነ መንገድ ምክንያት ሲሆን በዚህ ላይ ብዙ ጥሩ ነገር ተሰ ርቶአል፡፡ ወባ ለእናቶች ሞት ምክንያት እንደሚሆን እርግጥ ሲሆን የወባ መቀነስ ለእና ቶች ጤንነት መሻሻል አንዱ ምክንያት ነው፡፡ በቤተሰብ እቅድ አገልግሎት በኩል ከፍተኛ ስራ እየተሰራ በመሆኑ ወደ አምስት እጥፍ ያህል ሽፋኑ ጨምሮአል፡፡ ይህም የእናቶችን ጤና ለማሻሻል አስተዋጽኦ እንደሚኖረው ምንም አያጠያይቅም፡፡ የተባበሩት መንግስታት ጥናት እንደሚያሳየው የእናቶችን ሞት በመቀነስ ረገድ በኢት ዮጵያ ባለፉት ሀያ አመት ውስጥ በየአመቱ 4.9 ኀ ያህል እየቀነሰ መሆኑን ያሳያል፡፡ይህ ውጤት የሚያሳየን የል ማት ግቡን በጊዜው ልናሳካ ባንችልም እንኩዋን ጥሩ ውጤት መሆኑን መገንዘብ ይገባ ናል...ብለዋል፡፡”

Read 4769 times