Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Print this page
Saturday, 26 November 2011 08:54

ፀረ - ሴቶች ጥቃት ፊልሞች ይታያሉ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የታምራት ገዛኸኝ ሥዕሎች ዛሬ ይታያሉ
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የስፔን ኤምባሲና “UN Women” የሴቶችን ፆታዊ ጥቃት ለመዘከር የፊልም አውደ ርዕይ በጋራ እንዳዘጋጁ ተገለፀ፡፡
በዩኒቨርሲቲው ኤትኖግራፊክ ሙዚየም የሚቀርበው የፊልም አውደርእይ “ከጥቃት ነፃ ለሆነ ሕይወት በአንድነት” የሚል መልእክት ያዘለ ሲሆን ዛሬ በእውቋ ሶማሊያዊት ልእለ ሞዴል ዋሪስ ድሬ ሕይወትን አስመልክቶ የተሰራው “Desert Flowers” ለእይታ ይቀርባል፡፡ሰኞ “Take my Eyes” የተሰኘው የስፔን ፊልም የሚቀርብ ሲሆን ሌሎች ፊልሞችና የፎቶግራፍ አውደርዕይም ተዘጋጅቷል፡፡ የሰዓሊ ታምራት ገዛኸኝ ሥዕሎች ዛሬ ከቀኑ 9 ሰዓት ዘነበወርቅ አካባቢ በሚገኘው “ሌላ የሥዕል ጋለሪ” የሚከፈት ሲሆን እስከ ታህሳስ 8 ቀን 2004 ዓ.ም ከረቡዕ እስከ እሁድ ለሕዝብ ክፍት ሆኖ ይቆያል፡፡

Read 2574 times Last modified on Saturday, 26 November 2011 09:02

Latest from