Sunday, 24 November 2013 17:25

ዳሽን ባንክ ለ“መቄዶንያ” ግማሽ ሚሊዮን ብር ሰጠ

Written by  መንግሥቱ አበበ
Rate this item
(4 votes)

ዳሽን ባንክ መቄዶንያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማን መርጃ ማዕከልን “የዓመቱ ብቸኛው ምርጥ ግብረ ሰናይ ድርጅት” አድርጐ በመምረጥ፣ የ500ሺህ ብር ሽልማት ሰጠ፡፡   
ባንኩ፤ ማዕከሉ የሚያበረክተውን ማኅበራዊና ሰብአዊ አስተዋጽኦ በጥልቀት በማጤን፣ ማኅበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት፣ የተጠቀሰውን ገንዘብ እንዳበረከተ ገልጿል፡፡ አምናም ባንኩ ለ“መቄዶንያ” 200ሺ ብር መስጠቱ ይታወሳል፡፡
የአቅመ ደካማና ሕሙማን መርጃ ማዕከሉ፣ በአሁኑ ወቅት፣ ምንም ጧሪና ደጋፊ የሌላቸውን፣ በተለይም ራሳቸውን ችለው መፀዳዳት፣ መመገብና መንቀሳቀስ የማይችሉ ከ300 በላይ የአልጋ ቁራኛ አረጋውያንና የአዕምሮ ሕሙማንን ከወደቁበት ጐዳና በማንሳት፣ ተገቢውን እንክብካቤና ድጋፍ እያደረገ ሲሆን፤ በሚቀጥለው ዓመት የተረጂዎቹን ቁጥር 600 ለማድረስ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልጿል፡፡ ዕቅዱን ከግብ ለማድረስ እንዲረዳው ታኅሣሥ 13 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 9፡00 እስከ 12፡00 በግሎባል ሆቴል የገቢ ማሰባሰቢያ ማዘጋጀቱን የገለፀው ማዕከሉ፤ ለዚህ የተቀደሰ ዓላማ፣ ግለሰቦችና ድርጅቶች በስፍራው በመገኘት ድጋፍ እንዲያደርጉ በአረጋውያኑና በሕሙማኑ ስም ጠይቋል፡፡  


Read 1922 times