Saturday, 30 November 2013 10:38

ሞባይሌ ተወስዶብኛል በሚል የመግደል ሙከራ የፈፀመው 20 አመት ተፈረደበት

Written by  አለማየሁ አንበሴ
Rate this item
(3 votes)

ሞባይሌን ወስዶብኛል፤ ይመልስልኝ በሚል ሠበብ፣ የጁስ ቤት ሠራተኛ የሆነውን ግለሠብ በገጀራ በመምታት በጥርሡ
እና በአፍንጫው ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሠው ኢዮብ አድነው የተባለ ተከሣሽ፤ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ የ20 አመት ፅኑ

እስራት ተፈርዶበታል፡፡
በሌለበት የተከሠሠው አቶ ኢዮብ፤ የግል ተበዳይን ለመግደል አስቦ መስከረም 21 ቀን 2005 ዓ.ም በግምት ከምሽቱ 1

ሠአት ላይ በልደታ ክ/ከተማ፣ አብነት አደባባይ አካባቢ ወደሚገኝ ስሙ ያልተገለፀ ጁስ ቤት በማምራት፣ ወንጀሉን

መፈፀሙን የሚያሳዩ ማስረጃዎች አቃቤ ህግ አቅርቧል፡፡
ሠሞኑን የዋለው 10ኛ ወንጀል ችሎት፤ ተከሣሹ በሌለበት የአቃቤ ህግን 3 የሠው ማስረጃ መሠረት በማድረግ፣ “ክሡን

በሚገባ አልተከላከለም” በማለት ተከሣሹ በ20 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣና እስራቱን ሲጨርስ ለ3 አመታት

ከማንኛውም ህዝባዊ መብቱ እንዲታገድ በይኗል፡፡    

Read 2164 times