Print this page
Saturday, 07 December 2013 11:32

የኢትዮጵያን አየር ኃይል የ70 ዓመት ታሪክ የሚዘክር መጽሐፍ ሊታተም ነው

Written by  መታሰቢያ ካሳዬ
Rate this item
(3 votes)

በገቢ ማሰባሰቢያ 20ሚ. ብር ይጠበቃል

የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከተመሰረተበት 1913 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ደርግ ውድቀት 1983 ዓ.ም ድረስ ያለውን የሰባ አመት ታሪክ የሚዘክር መጽሐፍ ሊታተም ነው፡፡ ለመጽሐፉ ማሳተሚያና የአየር ኃይል ቬንተራንስ አሶሴሽንን ለማጠናከር በሸራተን አዲስ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ታህሳስ 24 ቀን 2006 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡ የአየር ኃይል ቬንተራንስ አሶሴሽን አመራር አባላት ሰሞኑን በድሪም ላይነር ሆቴል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተናገሩት፤ የአየር ኃይሉን የሰባ አመት ታሪክ ለመፃፍ ረጅም ጊዜ የወሰደባቸው ሲሆን ከአገር ውስጥና ከውጭ አገር የተገኙ መረጃዎችንና ቀደምት ፎቶግራፎችን በመጽሐፉ ለማካተት ከፍተኛ ጥረት ማድረጋቸውን ገልፀዋል፡፡

መጽሐፉ የተፃፈው ከደርግ ውድቀት በፊት በአየር ኃይሉ ይሰሩ በነበሩ ከፍተኛ የጦር መኮንኖች ሲሆን መጽሐፉን ለመፃፍ የሚያስችል መረጃ ለማሰባሰብ በሚደረገው ጥረት የአሁኑ አየር ኃይል አባላት ድጋፍ እንዳደረጉላቸው ተናግረዋል፡፡ በሸራተን አዲስ በሚካሄድ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም በሚገኘው ገቢ መጽሐፉን ለማሳተም እቅድ መያዛቸውን የገለፁት አመራሮቹ፤ መጽሐፉ ገበያ ላይ ውሎ የሚገኘውን ገቢ ለአየር ኃይል ቬንተራንስ አሶሴየሽን ማቋቋሚያና ማደራጃ ለማዋል ማሰባቸውንም ተናግረዋል። ከገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም 20 ሚሊዮን ብር እንደሚጠብቁም አመራሮቹ በዚሁ ወቅት ተናግረዋል።

Read 1757 times