Print this page
Saturday, 14 December 2013 10:42

85 ሚ.ብር የፈጀው ፒራሚድ ሆቴልና ሪዞርት ዛሬ ይመረቃል

Written by  ናፍቆት ዮሴፍ
Rate this item
(2 votes)

በቢሾፍቱ ከተማ ቢሾፍቱ ሀይቅ ዳርቻ ላይ የተገነባው “ፒራሚድ” ሆቴልና ሪዞርት ዛሬ ይመረቃል፡፡ 85 ሚሊዮን ብር የወጣበት ሪዞርቱ፤ ለግንባታ አምስት አመታትን የወሰደ ሲሆን ደረጃቸውን የጠበቁና ምቹ የመኝታ ክፍሎች፣ የህፃናት መጫወቻ፣ ዘመናዊ የስብሰባ አዳራሾች፣ ስፓ፣ ባርና ሬስቶራንቶች፣ የመዋኛ ገንዳ እና ላውንጅ እንዳሉት ታውቋል፡፡ ለ200 ሰዎች የስራ እድል ይፈጥራል የተባለው ፒራሚድ ሆቴልና ሪዞርት፤ ከፍተኛ የመንግስት ባስልጣናት፣ ባለሀብቶችና ታዋቂ ሰዎች በተገኙበት ዛሬ ከቀኑ 10 ሰዓት ተመርቆ ስራ እንደሚጀምር ለማወቅ ተችሏል፡፡ ፒራሚድ ሆቴልና ሪዞርት በቢሾፍቱ መሀል ከተማ ፒራሚድ የተሰኘ እህት ሆቴል አለውም ተብሏል፡፡

Read 1913 times