የቀድሞው የፓርላማ አባል “የተከበሩ አቶ ተመስገን ዘውዴ ህይወትና የፖለቲካ ቁጭት” በሚል ርዕስ የተዘጋጀውን መፅሀፍ የፃፈው አቶ ዳንኤል ተፈራ፤ በተለያዩ ጋዜጦች ላይ በመፃፍ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ ቀደም “ዳንዲ የነጋሶ መንገድ” የተሰኘ በዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ የህይወትና ፖለቲካ ጉዞ ላይ ያተኮረ መፅሀፍ መፃፉ ይታወሳል፡፡
የአሁኑ መፅሃፍም ከተከበሩ አቶ ተመስገን የትውልድ መንደር ጀምሮ ስለ ትምህርትና ፖለቲካ ጉዟቸው፣ ስለ ግንቦት ሰባት ምርጫና ስለ ፓርላማ ባልንጀሮቻቸው እንዲሁም ሌሎች ተያያዥ ታሪኮችን ያስቃኛል፡፡ 276 ገፆች ያሉት መፅሀፉ፤ በ27 ምዕራፎች የተከፋፈለ ሲሆን በ55 ብር በመሸጥ ላይ ይገኛል፡፡