በውድድሩ ላይ ከአለም ዙርያ 53 አገራትን የወከሉ ቆነጃጅት ተሳትፈው የውበት አክሊሉን የተቀዳጀችው ህንድን የወከለችው ናት፡፡ 17ኛው ሚስ ቱሪዝም ኪውን ኦፍ ዘ ይር በቻይና የጂንክሳይ ክልል ዋና ከተማ ይንግታን የተደረገ ሲሆን አላማው የአገራትን ወዳጅነት ለማጐልበት፤ የባህልና የልምድ ልውውጥ ለማድረግና ቱሪዝምን ለማስፋፋት በሚል ነው፡፡ ሚስ ዩክሬን፤ ሚስ ፖላንድ፤ ሚስ ማሌዝያና ሚስ ኮርያ እስከ አራተኛ’ ያለውን ደረጃ አከታትለው ወስደዋል፡፡