“ገፅ ሁለት” የተሰኘ እና በአራት ባለሙያዎች ተፅፎ ሁሉት ባሙያዎች ያዘጋጁት ትያትር ነገ ከቀኑ 11፡30 በሐገር ፍቅር ትያትር ቤት ይመረቃል፡፡ ተሻለ ወርቁ፣ ባዩሽ አለማየሁ፣ ዝናሽ ጌታቸው እና ብሌን ጌታቸው የፃፉትን ድርሰት አብዱልከሪም ጀማል እና አለምፀሃይ እጅጉ አዘጋጅተውታል፡፡ ትዕግስት ግርማ፣ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ሂሩት ኪሮስ፣ ብዙወርቅ ዋቅቶላ፣ እና አለምፀሃይ እጅጉ ተውነውበታል፡፡ ከፀሃፊዎቹ ሁለቱ በሃገር ውስጥ እንደሌሉ ይታወቃል፡፡ በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩረው ትያትር መሆኑም ታውቋል፤ “ገፅ ሁለት”፡፡