Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Print this page
Saturday, 03 December 2011 08:43

አርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም ዛሬ ወጣቶችን ይመክራል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የቲቢ አምባሳደር በመሆን ቅስቀሳ በማድረግ ላይ የሚገኘው አንጋፋው አርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም ዛሬ ቦሌ በሚኘው ሲዮናት ሆቴል የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎችን እንዲሁም በማረሚያ ቤትና በሐይማኖት ተቋማት የሚገኙ ሌሎች ዜጐችን ይመክራል፡፡ ከጤና ጥበቃ ሚኒስቴር፤ ከዓለም ጤና ድርጅት (WHO) እና ከመሠል ድርጅቶች ጋር እየሰራ ያለው አርቲስቱ “መስኮት በመክፈት ቲቢን እንከላከል” በሚል ቅስቀሳ እያደረገ መሆኑ ይታወቃል፡፡ የአሁኑን የምክክር መድረክ ያዘጋጁት ከዩኤስ ኤ አይዲ በተገኘ ድጋፍ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር እና ቲቢ ኬር ኢትዮጵያ ከቲቢ ሚዲያ ፎረም ጋር በመሆን ሲሆን ት/ቤቶች፣ ማረሚያ ቤትና የሃይማኖት ተቋማት ለቲቢ ስርጭት ይበልጥ ተጋላጭ ስለሆኑ ነው የተሻለ ጥንቃቄ ለመውሰድ በሚል ምክክሩ ያስፈለገው ተብሏል፡፡

ይህ በዚህ እንዳለ የአንጋፋው አርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም ተመሳሳይ አላማ ያለው ቢልቦርድ በመጪው ረቡዕ በባህር ዳር ከተማ ይመረቃል፡፡ አርቲስቱም ቢልቦርዱን ካዘጋጀው አይቴክ ኢትዮጵያ ጋር በመሆን ምርቃቱ ላይ ለመገኘት ወደ ባህር ዳር የሚጓዝ ሲሆን ተመሣሣይ የፀረ ቲቪ ቅስቀሳ እንደሚያደርግ ይጠበቃል፡፡ በሌላም በኩል አርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም ባለፈው ረቡዕ ጉርድ ሾላ አካባቢ በሚገኘው ሉሲ ዩዝ አካዳሚ “ከበደ ሚካኤል የንባብና የውይይት ክበብ” በመገኘት የትምህርት ቤቱን ተማሪዎችና ወደ ትወና ጥበብ መግባት የሚፈልጉ ወጣቶችን በመምከር አበረታትቷል፡፡ አርቲስቱ በተጨማሪም ተጫውቷቸው ከነበሩ ተውኔቶች የሁለቱን ቃለ ተውኔት በመቀንጨብ ለተማሪዎቹ አስደምጧል፡፡ የትምህርት ቤቱ የንባብና የውይይት ክበብ፣ ባለፈው ወር ኢንጂነር ታደለ ብጡል ክብረትንና ጋዜጠኛ በፍቃዱ አባይን ጋብዞ የነበረ ሲሆን ለትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ ኪነጥበባዊ ልምዳቸውን እንዳጋሩና ዝግጅቱ በየወሩ እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል፡፡

 

Read 2496 times Last modified on Saturday, 03 December 2011 08:44

Latest from