Saturday, 18 January 2014 11:24

“...በወንድ ህፃናት ላይ የሚደርስ የወሲብ ጥቃትና ብዝበዛ...”

Written by  ፀሐይ ተፈረደኝ (ከኢሶግ)
Rate this item
(7 votes)

“...በአሁን ወቅት ዕድሜው 22 ዓመት ነው። የወሲብ ጥቃቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈፀመበት ግን የ10 ዓመት ልጅ በነበረ

ጊዜ ነው፡፡ የዚህ ታሪክ ባለቤት የሆነው ህጻን ሁለቱም ወላጆቹ በህይወት አሉ፤ በጣም ጥሩ የገቢ ምንጭ ያላቸውና

በተለምዶ ሃብታም ቤተሰብ የሚባሉ የአዲስ አበባ ኗሪ ናቸው፡፡ ሆኖም ወላጆቹ ወደ ንግድ ሥራቸው እንጂ ከልጁ ጋር

የቅርብ ክትትልና በግልፅ የመነጋገር ልምድ አልነበራቸውም፡፡ የ10 ዓመት ህፃን እያለ አንድ ወንድ አስጠኚ ተመድቦለት

እቤት ውስጥ ሁለቱንም ብቻቸውን በመተው ወላጆቹ ወደ ሥራ ይሄዱ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ነበር አስጠኚው የወሲብ ጥቃት

በህፃኑ ላይ የፈፀመበት፤ ይህ ድርጊት ተጠቂው 15 ዓመት እስኪሆነው ድረስ ቢቀጥልም ወላጆች ምንም የሚያውቁት ነገር

አልነበረም፡፡ ለአምስት ዓመታት ጥቃት ከፈፀመበት በኋላ ጥቃት ፈፃሚው አሜሪካን ሃገር ሄዷል፡፡ ጥቃት የተፈፀመበት

ልጅ ድርጊቱ ጥቃት መሆኑን ዘግይቶ ተረድቷል፤ ውስጡ የብቀላ ስሜት አድሮበታል፤ ቤተሰቦቹን ደጋግሞ ቢረግምም

የደረሰበትን ጉዳት በሚመለከት ምንም አልገለፀላቸውም፤ ራሱን እንደ ወራዳ፤ ቆሻሻ በመቁጠር የህይወት ትርጉም እንዳጣ

ገልጧል፡፡ አንዳንዴ ራሱን የማጥፋት ስሜት ይሰማዋል፡፡
በላይ ሓጎስ አዲሰ አበባ ዩኒቨርሲቲ
ሓምሌ 27 ቀን 2002 ዓ.ም.
ከላይ ያነበባችሁትን መረጃ ያገኘነው ከበላይ ሐጎስ ጥናት ነው፡፡ ይህን አምድ በዚህ ጥናት መነሻነት መረጃ ያቀረብንበት

ምክንያትም የተለያዩ አንባቢዎች ከአሁን ቀደም ለንባብ ቀርበው የነበሩ ጽሁፎችን መነሻ በማድረግ ያቀረቡዋቸውን

ጥያቄዎች መነሻ በማድረግ ነው፡፡ ቀደም ሲል ለንባብ ቀርቦ የነበረው ሴት ህጻናት በወሲብ ጥቃት በሚደርስባቸው ጊዜ

በአንድ የህክምና ተቋም ውስጥ በሚቋቋም ማእከል የህክምና የፍትህ እና ስነልቡና አገልግሎት እንደሚሰጣቸውና

ባለጉዳዮቹ መንገላታት ሳይደርስባቸው ጥቃት አድራሹ ወደ ህግ የሚቀርብበት አሰራር ከአንድ አመት ወዲህ እንደተ

ጀመረ ይገልጸል፡፡ ሆኖም ግን ወንድ ልጆችን በሚመለከት ይህ አሰራር የሌለ ሲሆን ወንዶች የወሲብ ጥቃት

ቢደርስባቸው ሊታከሙ የሚችሉት በጠቅላላ ሐኪም ወይንም በቀዶ ሕክምና ባለሙያ መሆኑን ያመለክታል፡፡ ከዚህም

በመነሳት አንዳንድ ጥያቄዎች ተሰንዝረዋል፡፡ ከጥያቁዎቹም መካከል...
የወንዶች ልጆች የወሲብ ጥቃት ምን ያህል አሳሰቢ ነው?
ወንድ ልጄ ተገዶ በመደፈሩ በእርግጥ ሕክምናውን አግኝቶአል፡፡ ነገር ግን እስከአሁን ድረስ መንፈሱ ትክክል አይደለም።

ለምንድነው?
ለምን ለወንዶቹስ እንደሴቶቹ የተለየ ተቋም አይዘጋጅላቸውም? የሚሉ ይገኙበታል፡፡
ጥያቄዎቹ የሚጠቁሙዋቸውን ነጥቦች በትክክል መልስ ባይሰጥም ነገር ግን የበላይ ሐጎስ (አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ) የዳሰሳ

ቅኝት ስለሁኔታው ያነሳቸውን ጠቃሚ ሀሳቦች ለአንባቢ ብለናል፡፡
ከፖሊስ የተገኘ መረጃ እንደሚያመለከተው በአስሩም ክፍለ ከተሞች የህፃናት እንክብካቤ ማዕከላት በ1996 ዓ.ም.

የወሲብ ጥቃት ደርሶባቸው ጉዳያቸው ለፖሊስ ሪፖርት የተደረገ 47 ወንድ ህፃናት ዝርዝር መረጃ ተተንትኗል፡፡

በተጨማሪም በአንፕካን ኢትዮጵያ እርዳታ ሲያገኙ የነበሩት 13 የወሲብ ጥቃት ሰለባ የሆኑ ወንድ ህፃናት መረጃንም

አካትቷል፡፡
የጥናቱ ግኝት ጥቃቱ የደረሰባቸው ወንድ ህፃናትን በሚመለከት የሚከተሉትን ነጥቦች በዝርዝር አስቀምጦአል፡፡
- በ1996 ዓ.ም. የወሲብ ጥቃት የደረሰባቸው ህፃናት ጉዳይ ለፖሊስ ሪፖርት የተደረገው 218 ነበር፡፡ ከዚህ ውስጥ 47ቱ

ማለትም 22% በወንድ ህፃናት ላይ የደረሰ ነበር፡፡
- 51% የሚሆኑት ጥቃት የደረሰባቸው ህፃናት ጉዳታቸውን ለፖሊስ እራሳችው ሪፖርት ያደረጉ ሲሆኑ፤ 34% ሪፖርት

የተደረገው በወላጆቻቸው ነበር፡፡ በአንፃሩ 3% ብቻ ነበር በፖሊስ ክትትል የታወቀው፡፡
- ይብዛም ይነስም በአስሩም ክፍለ ከተሞች በወንድ ህፃናት ላይ የወሲብ ጥቃት ተፈፅሟል፡፡
የጥቃቱ ሰለባ ወንድ ህፃናት ዕድሜአቸው ከ3-18 ዓመት ነበር፡፡ 77% የሚያህሉ ከ1ኛ እስከ 8ኛ ክፍል የደረሱ ተማሪዎች

ነበሩ፡፡
- አብዛኛው ማለትም 89% ጥቃት የደረሰባቸው ህፃናት ከአልኮልና እፆች ልምድ ነፃ ነበሩ፡፡ ነገር ግን 6% የሚያህሉ  

የአልኮልና እፆች መጠቀም ልምድ ነበራቸው፡፡
- ጥቃቱ የደረሰባቸው በልዩ ልዩ ሰዎች ሲሆን 45% ያህሉ በጎረቤቶቻቸው፤ 36% በማይታወቁ ሰዎች፤ እንዲሁም 19%

በተለያዩ ሰዎች ጥቃት ደርሶባቸዋል፡፡
ከላይ የተገለጸው መረጃ በወንዶች ላይ የሚደርስ የወሲብ ጥቃት ምን ያህል አሳሳቢ ነው? ለሚለው ጥያቄ ምላሽ

ይሰጣል፡፡ ይህ ጥናት በተካሄደበት ጊዜ መረጃው የተሰበሰበው ከ1996 ዓ/ም ዶክመንት ሲሆን ከዚያ ወዲህ ያለውን

እውነታ ለማገናዘብ ይረዳል፡፡
ጥናቱ እንደሚጠቁመው ከተለያዩ የህብረተሰቡ ክፍሎች የተሰበሰቡት አስተያየቶች የሚከተሉት ናቸው፡፡  
ወሲባዊ ጥቃት በወንድ ህፃናት ላይ ይከሰታል ብሎ የሚገምት ኢትዮጵያዊ ወላጅ እስከቅርብ ጊዜ አልነበረም ለማለት

ያስደፍራል፡፡ ከዚህ ጥናት በኋላም ቢሆን አብዛኛው ወላጅም ሆነ ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍል ምንም ግንዛቤ የሌለው

መሆኑ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል፡፡
አንዲት እናት እንዳሉት የሴት ልጄን የወሲብ ጥቃት እንዳይደርስባት ከመስጋት ውጪ ወንድ ልጄ ለአፍታም ቢሆን

የወሲብ ጥቃት ይደርስበታል የሚል ጥርጣሬ አልነበረኝም ብለዋል፡፡
ይህ የብዙ ወላጅ ግምት ሲሆን በዚህ ጥናት የተዳሰሰው ግኝት ደግሞ ወላጆችንም ሆነ ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን

ግምታቸውን እንዲያስተካክሉ የሚያሳስብ ነው፡፡ ይላል የጥናት ወረቀቱ፡፡
ወንድ ህፃናት ለወሲብ ጥቃት ተጋላጭ የሚሆንባቸው ምክንያቶች፤
- ተጋላጭ አኗኗር
የቤተሰብ/የአሳዳጊ ትኩረት እና ክትትል ያለማግኘት፤
ከቤተሰብ ጋር በግልፅ የመወያየት ልምድ ያለመኖር፤
ተቀራርቦ መተኛት፤
ተገቢ መረጃ ያለማግኘት፤
በራስ የመተማመን ብቃት የሌለቸው ህፃናት፤
አሳዳጊና ተንከባካቢ የሌላቸው ህፃናት ...ወዘተ ናቸው፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ በወንድ ህፃናት ላይ የደረሰው ወሲባዊ ጥቃት ያስከተለው ጉዳት፤
- አካላዊ ጉዳት፡-
የፊንጢጣ ማሳከክ፤
የአባለዘር በሽታ በአፍና በፊንጢጣ ላይ መገኘት፤
የብልት ማበጥ
- ሥነ-ልቦናዊ ጉዳት፡
የወሲብ ህይወት ተበላሽቶብኛል ብሎ የመቆጨትና የመፀፀት፤
የወሲብ ስሜቴ ወደ ሴት ሳይሆን ወደ ወንድ ያደላብኛል ብሎ የመስጋት፤
ራስን ዝቅ የማድረግና ራስን የመጥላት ስሜት፤
ራስን የማጥፋት ስሜትና ሙከራ፤
ከተለመደው ሥፍራ የመጥፋት ስሜት እና ለመጥፋት መሞከር፤
የመፍራትና የመጨነቅ ስሜት፤ ኤችአይቪ ይዞኝ ይሆናል ብሎ መጨነቅ፤
በወንድ ህፃናት ላይ የብቀላ ስሜት፤
የመጣላትናት የመጋጨት ስሜት፤
ከእድሜው የማይጠበቅ የወሲብ ነክ አገላለፆችንና ድርጊቶችን መፈፀም፤
ከዚህም በተጨማሪ ጉዳቱ ማህበራዊና ስነልቡናዊ ቀውስን የሚያስከትል ሲሆን መገለጫዎቹም...
ማህበራዊና ሥነ-ልቦናዊ ቀውስ፡
ሰዎችን መጠራጠር ሰዎች ስለኔ ይወያያሉ /ያወራሉ ብሎ መገመት/ መጨነቅ፤ ሰዎች ያርቁኛል ብሎ መስጋት፤ ከሰዎች

መራቅ፤ መለየት፤ መገለል፤
በትምህርት ላይ የሚያስከትለው ተፅዕኖ፡
ትምህርት ለመከታተል መቸገር፤ ትኩረት ማጣት፤ ከትምህርት መቅረት፤ ማቋረጥ፤ ምትመህርት ዝቅተኛ ውጤት

ማግኘት፤ ከክፍል ወደ ክፍል ለመዛወር መቸገር፤ ክፍል መድገም ከክፍል ጓደኞች ጋር ለመቀራረብ መቸገር...

የመሳሰሉትን ጉዳቶች ያስከትላል የበላይ ሐጎስ የጥናት ዳሰሳ እንደሚያስረዳው፡፡ 

Read 13594 times