Monday, 27 January 2014 08:58

“ግጥምን በማሲንቆ” የተሰኘ ፕሮግራም ተካሄደ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ካለፈው አመት ጀምሮ መቅረብ የጀመረው “ግጥምን በማሲንቆ” ባለፈው ሳምንት በጎንደር ተካሄደ፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ ጐንደር ከተማ በሚገኘው አፄ በካፋ ሆቴል አዳራሽ የተካሄደው ፕሮግራሙ፣  በየአመቱ በወርሃ ጥር በጥምቀት መዳረሻ ላይ እንደሚካሄድ የፕሮግራሙ አዘጋጅ ገጣሚ ትዕግስት ሲሳይ ተናግራለች፡፡ በዝግጅቱ ላይ ገጣሚና ፀሐፌ ተውኔት ጌትነት እንየው፣ ገጣሚና ጋዜጠኛ ባንቻየሁ አለሙና በርካታ ወጣት  ገጣሚያን ስራዎቻቸውን አቅርበዋል፡፡ ግጥምና ማሲንቆ አንዳቸው ያለ አንዳቸው መኖር አይችሉም ያለችው አዘጋጇ፣ፕሮግራሙን የማስፋፋት አላማ እንዳላት ተናግራለች፡፡

Read 1540 times