Monday, 27 January 2014 09:12

“ጽሞና እና ጩኸት” ዛሬ፤“ማርሲላስ” ነገ ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በገጣሚ ሰሎሞን ሞገስ /ፋሲል/ የተጻፈው “ጽሞና እና ጩኸት” የተሰኘ የግጥም መድበል ዛሬ ከጠዋቱ 2 ሰዓት ከ30 ጀምሮ በጣይቱ ሆቴል የጃዝ አምባ ማዕከል ይመረቃል። የገጣሚው ሶስተኛ ስራ የሆነው መጽሃፉ፤76 ገጾች ያሉት ሲሆን በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥኑ 59 ግጥሞችን አካቷል፡፡ የመሸጫ ዋጋውም 20 ብር ነው፡፡
ገጣሚው ከዚህ በፊት ‘እውነትን ስቀሏት’ እና ‘ከጸሃይ በታች’ የተሰኙ የግጥም መፃህፍትን ለንባብ ያበቃ ሲሆን በተለያዩ የስነጽሁፍ መድረኮች ላይ ግጥሞቹን በማቅረብም ይታወቃል፡፡ በሌላ በኩል በህግ ባለሙያዋ ሂሩት ምህረት የተጻፈው “ማርሲላስ” የተሰኘ የረጅም ልቦለድ መጽሐፍ ነገ ማለዳ በሐገር ፍቅር ቲያትር አዳራሽ ይመረቃል፡፡ ለፀሃፊዋ የመጀመሪያ ስራዋ የሆነውና በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተው ልቦለዱ፤270 ገጾች ያሉት ሲሆን፣ በ75 ብር በተለያዩ የመጽሃፍት መደብሮችና በአዟሪዎች እየተሸጠ ይገኛል፡፡

Read 2289 times