Monday, 27 January 2014 09:14

“ባቢሎን” ለህዝብ እየታየ ነው

Written by 
Rate this item
(2 votes)

በጋዜጠኛ ሸዋዬ ገላው ተጽፎ፣ በራሱ በሸዋዬና በደመወዝ ጎሽሜ የተዘጋጀው “ባቢሎን” የተሰኘ ኮሜዲ ፊልም በሳምንቱ መጀመሪያ በተለያዩ ሲኒማ ቤቶች ለእይታ በቃ፡፡
የአንድ ሰዓት ከአርባ ደቂቃ ርዝማኔ ያለው ፊልሙ፤ በብድር ባገኙት ገንዘብ የኤሌክትሪክ ምጣድ በማደስ ራሳቸውን ለመለወጥ የሚተጉ ጓደኛሞች የሚገጥሟቸውን ፈተናዎች የሚያሳይ ሲሆን  ሰርቶ ለመጨረስ አንድ አመት ከመንፈቅ ፈጅቷል፡፡ በፊልሙ ላይ አሰፋ በየነ፣ ሰላም ይሁን አስራት፣ በረከት በላይነህ (አመዶ)፣ ትዕግስት በጋሻው፣ እንግዳ ጌታቸው እና ሌሎች ተዋንያን ተሳትፈውበታል። ጋዜጠኛ ሸዋዬ ገላው በ“ገመና 2” ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ላይ በደራሲነት ተሳትፏል፡፡

Read 2537 times