Monday, 03 February 2014 12:38

5 የጉዞ አድዋ አባላት ወደ አድዋ እየገሰገሱ ነው

Written by 
Rate this item
(4 votes)

ከአስራ አራት ቀን በፊት “አድዋ ይከበር ይዘከር ለዘላለም” በሚል መሪ ቃል ከአዲስ አበባ ጣይቱ ሆቴል የእግር ጉዞ የጀመሩት የጉዞ አድዋ አባላት፤ የካቲት 23 ታሪካዊቷ አድዋ አምባ እንደሚደርሱ ለአዲስ አድማስ ገለፁ፡፡ ወደ አድዋ የሚያደርጉትን ታሪካዊ ጉዞ ከመጀመራቸው በፊት በዶ/ር አኧዘ ጣዕመ፣ ሙሉ የጤንነት ምርመራ የተደረገላቸው ሲሆን “ዘ አዘር ፌስ ኦፍ ኢትዮጵያ” ሙሉ ወጪያቸውን እንዲሁም አዲካ ለቀረጻ የሚያገለግላቸውን መኪና እንዳበረከተላቸው ከተጓዦቹ አንዱ የሆነው አርቲስት መሃመድ ካሣ ገልጿል፡፡

የጉዞው ዓላማ የአድዋ ጀግኖችን መዘከርና እነሱ የተጓዙበትን አስቸጋሪ መንገድ ማስታወስ ሲሆን አባላቱ የጉዞ መስመራቸውን ያደረጉትም አጼ ሚኒልክ ጦራቸውን ከአዲስ አበባ ይዘው በወጡበት መንገድ ነው ብሏል - አርቲስት መሃመድ፡፡ በዛሬው እለት ከአዲስ አበባ ከ400 ኪሎ ሜትር በላይ በምትርቀው ሀይቅ ከተማ የሚደርሱ ሲሆን የጉዞው ፍጻሜ የአድዋ በዓል ዕለት የካቲት 23 ቀን 2006 ዓ.ም ይሆናል፡፡ የጉዞው አባላት መሃመድ ካሳን ጨምሮ 5 ሲሆኑ የኢትዮፒካ ሊንክ ሬዲዮ ፕሮግራም አዘጋጅ ብርሃኔ ንጉሴ እንዲሁም ኤርሚያስ አለሙ፣ ሙሉጌታ መገርሣ (አማሩ) እና አለም ዘውዱ ካሣሁን ይገኙበታል፡፡በጉዟቸው የጤና እክል እንዳላጋጠማቸው የገለጹት የጉዞው አባላት፤ በዶ/ር አኧዞ የቅርብ ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

Read 1539 times