Monday, 03 February 2014 12:44

አዲሱ የጋዜጠኞች ማህበር አመራሮቹን መረጠ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በቅርቡ የተቋቋመው “የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ” ከትናንት በስቲያ ጠቅላላ ጉባኤውን አካሂዶ የማህበሩን የመተዳደሪያ ደንብ ያፀደቀ ሲሆን አመራሮቹንና የስራ አስፈጻሚ አካላትንም መርጧል፡፡ ጋዜጠኛ በትረ ያዕቆብ ሊቀመንበር፣ ጋዜጠኛ ስለሺ ሃጐስ ምክትል ሊቀመንበር እንዲሁም ጋዜጠኛ ነብዩ ሃይሉ ዋና ፀሃፊ በመሆን የተመረጡ ሲሆን ጋዜጠኛ አያሌው አስረስ የማህበሩ ጠቅላላ ጉባኤ አፈ-ጉባኤ፣ ጋዜጠኛ ጌታቸው ወርቁ ምክትል አፈ-ጉባኤ እንዲሁም ጋዜጠኛ ብሩክ ከበደ የአፈ-ጉባኤ ፀሃፊ ሆነው እንደተመረጡ ለማወቅ ተችሏል፡፡ አዲስ የተመረጡት አመራሮች በጋራ በሰጡት መግለጫ፤ማህበሩ ሙያተኛውን ብቻ ማዕከል አድርጐ በመንቀሳቀስ የአባላቱን መብት እንደሚያስከብር፣የአባላቱን ሙያዊ ክህሎት በተለያዩ ስልጠናዎች እንደሚያዳብርና ሃሣብን በነጻነት የመግለጽ መብትን በተሟላ መልኩ ለማስከበር በትጋት እንደሚሰራ ጠቁመዋል፡፡ አዲሱን የጋዜጠኞች ማህበር ማቋቋም ያስፈለገው በአገሪቱ ውስጥ የሚንቀሳቀሱ የጋዜጠኞች ማህበራት የሙያተኛውን መብት በቅጡ ማስከበር ባለመቻላቸው ነው መባሉ ይታወሳል፡፡

Read 1725 times