Monday, 03 February 2014 13:39

ህገ-ደንቦች ላይ ያተኮረው መጽሃፍ ለገበያ ቀረበ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

“ድብቆቹ ህገ-ደንቦች! የጽዮናውያን አለሙን የመቆጣጠር እቅድ ሰነድ” የተሰኘውና በግደይ ገ/ኪዳን የተዘጋጀው መጽሃፍ ሁለተኛ ጥራዝ ለገበያ ቀረበ፡፡ ደራሲው ከዚህ ቀደም 24 ህገ ደንቦች የያዘውን የመጽሃፉን የመጀመሪያ ክፍል ለአንባቢያን ያቀረበ ሲሆን በዚህኛው የመጽሃፉ ክፍል ስለ ህገ-ደንቦች ታሪካዊ አመጣጥ እንዲሁም ህገ-ደንቦች እውነተኛ ናቸው፣ ወይንስ የግምት የሚሉ መከራከሪያ ሃሣቦች እንደተካተቱ ተጠቁሟል፡፡ ደራሲው ከዚህ ሌላ “ጥንታዊ ውጊያ”፣ “ህልም አጨናጋፊዎቹ”፣ “የአሜሪካ የሚስጥር ተቋም” በሚሉ ሥራዎቹም ይታወቃል፡፡

Read 2221 times