Monday, 03 February 2014 13:41

የአርቲስት ሽመልስ አራርሶን የህይወት ታሪክ የሚዘክረው ፊልም ይመረቃል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የሚውዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ መሥራች የነበረው የአርቲስት ሽመልስ አራርሶን የህይወት ታሪክ የሚዘክረው ፊልም

የፊታችን ሐሙስ በጣይቱ ሆቴል ጃዝ አምባ አዳራሽ ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በሚካሄድ ስነ ስርዓት ይመረቃል፡፡
የአርቲስቱን 7ኛ የሙት ዓመት መታሠቢያ ምክንያት በማድረግ በቁም ነገር ሚዲያ ስቱዲዮ የተዘጋጀው ዘጋቢ ፊልም፤

የአርቲስቱ  የህይወት ጉዞና ሥራዎች ላይ ያተኩራል ተብሏል፡፡ በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ስለአርቲስት ሽመልስ አራርሶ

የሙያ ምስክርነትና ልዩ ልዩ ኪነ-ጥበባዊ ዝግጅቶች የሚቀርቡ ሲሆን በኤክስኘረስ ባንድ ጣዕም ያላቸው ሙዚቃዎችም

ይቀርባሉ ተብሏል።

Read 1711 times