የሚውዚክ ሜይዴይ ኢትዮጵያ መሥራች የነበረው የአርቲስት ሽመልስ አራርሶን የህይወት ታሪክ የሚዘክረው ፊልም
የፊታችን ሐሙስ በጣይቱ ሆቴል ጃዝ አምባ አዳራሽ ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በሚካሄድ ስነ ስርዓት ይመረቃል፡፡
የአርቲስቱን 7ኛ የሙት ዓመት መታሠቢያ ምክንያት በማድረግ በቁም ነገር ሚዲያ ስቱዲዮ የተዘጋጀው ዘጋቢ ፊልም፤
የአርቲስቱ የህይወት ጉዞና ሥራዎች ላይ ያተኩራል ተብሏል፡፡ በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይ ስለአርቲስት ሽመልስ አራርሶ
የሙያ ምስክርነትና ልዩ ልዩ ኪነ-ጥበባዊ ዝግጅቶች የሚቀርቡ ሲሆን በኤክስኘረስ ባንድ ጣዕም ያላቸው ሙዚቃዎችም
ይቀርባሉ ተብሏል።
Monday, 03 February 2014 13:41
የአርቲስት ሽመልስ አራርሶን የህይወት ታሪክ የሚዘክረው ፊልም ይመረቃል
Written by Administrator
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና