Monday, 10 February 2014 07:43

የኢራን የፊልም ፌስቲቫል ተካሄደ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በኢትዮጵያ የኢራን ኢምባሲ የባህል ክፍል የሚዘጋጀው አመታዊው የኢራን የፊልም ፌስቲቫል ካለፈው ሰኞ ጀምሮ በብሄራዊ ትያትር ተካሄደ፡፡
የኢራንን እስላማዊ አብዮት 35ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ የተከናወነው ይህ የፊልም ፌስቲቫል፣ የሁለቱን አገራት ባህላዊ ግንኙነት የማጠናከርና የኢራን የፊልም ኢንዱስትሪ የደረሰበትን ደረጃ የማስተዋወቅ አላማ እንዳለው በኢትዮጵያ የኢራን አምባሳደር አሊ ባህሪኒ በፌስቲቫሉ መክፈቻ ላይ ተናግረዋል፡፡ የኢራን ኢምባሲ የባህል ክፍል፣ በሁለቱ አገራት መካከል የተፈረመውን የባህል፣ የትምህርትና የሳይንስ ትብብር መሰረት በማድረግ የኢትዮጵያን ፊልም ለማሳደግ የሚያግዙ ስራዎችን እንደሚያከናውንም ገልጸዋል፡፡
ለሶስት ተከታታይ ቀናት በተካሄደው በዚህ የፊልም ፌስቲቫል ላይ፣ ‘ኤም ፎር ማዘር’፣ ‘ዘ ሶንግስ ኦፍ ስፓሮውስ’ እና ‘ኦን ፉት’ የተሰኙ፣ በአለማቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያገኙ ስኬታማ የኢራን ፊልሞች ለእይታ በቅተዋል፡፡

Read 1767 times