Print this page
Monday, 10 February 2014 07:47

‘ድፍረት’ ፊልም ተሸለመ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

በኢትዮጰያዊው ፊልም ባለሙያ ዘረሰናይ ብርሃኔ ተጽፎ የተዘጋጀው ድፍረት ፊልም፣ በ2014 ሰንዳንስ አለማቀፍ የፊልም ፌስቲቫል በ‘ወርልድ ሲኒማ ድራማቲክ ኦዲየንስ’ ዘርፍ ተሸላሚ ሆነ፡፡
ታዲያስ መጽሄት ከኒዮርክ እንደዘገበው፣ በእውነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የተሰራውና የ99 ደቂቃ ርዝማኔ ያለው የዚህ ፊልም ዳይሬክተር ዘረሰናይ ብርሃኔና ፕሮዲዩሰሯ ምህረት ማንደፍሮ ባለፈው ቅዳሜ በተከናወነው የፌስቲቫሉ የመዝጊያ ስነስርዓት ላይ ተገኝተው ሽልማቱን ተቀብለዋል፡፡
በሰንዳንስ አለማቀፍ የፊልም ፌስቲቫል ላይ በመካፈል የመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ፊልም የሆነውና በተለያዩ የአሜሪካ ሲኒማ ቤቶች ተዘዋውሮ ሲታይ የሰነበተው ድፍረት፣ በተመልካቾች ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነት በማግኘቱ ነው በዘርፉ ተሸላሚ ለመሆን የበቃው፡፡
ከፊልሙ ኤክስኪዩቲቭ ፕሮዲዩሰሮች አንዷ የሆነችው ታዋቂዋ የሆሊውድ የፊልም ተዋናይት አንጀሊና ጆሊ፣ ከሳምንታት በፊት ድፍረት በኢትዮጵያ የፊልምና የኪነጥበብ ዘርፍ ላይ የራሱን አሻራ ያሳረፈ ስራ ነው ስትል አድናቆቷን መግለጧ ይታወሳል፡፡

Read 3543 times
Administrator

Latest from Administrator