Saturday, 15 March 2014 13:19

“ስንክርተነ” የተባለ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የጉራጊኛ የግጥም መፅሀፍ ነገ-ይመረቃል
የቤተ ጉራጌ ባህል ማዕከል ዋና ስራ አስኪያጅ በሆኑት በአቶ ተስፋዬ ጐይቴ የተፃፈው “ስንክርተነ” የተባለ የግጥም መፅሀፍ ነገ በደሳለኝ ሆቴል ይመረቃል። 135 ግጥሞችን ያካተተውና በ140 ገፆች ላይ የተመጠነው መፅሀፉ፤ በጉራጊኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ሲሆን አብዛኞቹ ግጥሞች የጉራጌን ባህል፣ ወግና ትውፊት ያስቃኛሉ ተብሏል፡፡ ትልቁን የነፃነት ታጋይ የኔልሰን ማንዴላን ህይወት የተመለከተ ረጅም ግጥም እንደተካተተበትም አቶ ተስፋዬ ጐይቴ ገልፀዋል፡፡
በ33 ብር ለገበያ የቀረበው መፅሀፉ፤ በሴትኛ አዳሪነት ህይወት እና በሌሎችም ማህበራዊ ህይወት ላይ ትኩረት ያደረገ ሲሆን ፀሀፊው ከዚህ በፊት “የኬርጋት” እና “ጉራጌንዶ” የተሰኙ የግጥም መፃህፍትን በጉራጊኛ ቋንቋ ፅፈው ለንባብ አብቅተዋል።
ሶስተኛውና “ስንክርተነ” የተሰኘው የግጥም መፅሀፍ ነገ ጠዋት ከ2፡30 ጀምሮ ባለስልጣናት፣ የባህልና ቱሪዝም ሀላፊዎች፣ ጋዜጠኞችና ጥሪ የተደረገላቸው ሌሎች እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ይመረቃል ተብሏል፡፡

Read 1640 times