በጋዜጠኛ ግርማ ለማ የተፃፈውና በቀዳማዊ ሀ/ስላሴ የቤት ውስጥ ውሎ፣ ቤተሰባዊ ህይወትና የጓዳ ታሪክ ላይ የሚያጠነጥነው “የንጉሱ ገመና” ለንባብ በቅቷል፡፡
መፅሀፉ እስከ ዛሬ በንጉሱ ዙሪያ ከተፃፉት መፅሀፎች የሚለየው በቤት ውስጥ ውሏቸውና ገመናቸው ላይ የሚያተኩር በመሆኑ ነው ተብሏል፡፡ 170 ገፆች ያሉት መፅሀፉ፤ በአርጋኖ የህትመት ኢንዱስትሪ ታትሞ በጃፋር መፅሀፍ መደብር እየተከፋፈለ ሲሆን በ49 ብር ከ75 ሳንቲም ለገበያ መቅረቡም ታውቋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና