Saturday, 15 March 2014 13:23

“የህይወት ኮስሞቲክስ” የግጥም መድብል ገበያ ላይ ዋለ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

        66 አጫጭር ግጥሞችን ያካተተውና በተማሪ ማንያዘዋል እሸቱ የተፃፈው “የህይወት ኮስሞቲክስ” የግጥም መድበል ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡
በ66 ገፆች የተቀነበበው የግጥም መድበሉ፤ ተማሪው ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ ያሰባሰባቸው ግጥሞች የተካተቱበት ሲሆን በማህበራዊ፣ በፍቅር፣ በአገር፣ በወጣትነት፣ በካምፓስ ህይወትና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥን እንደሆነ ታውቋል፡፡
በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የሁለተኛ አመት የኢንቫይሮንሜንታል ኢንጂነሪንግ ተማሪ የሆነው ገጣሚው፤ የፊልም ስክሪፕት የመፃፍ ስራ ላይ ማተኮሩን ገልፆ የመጀመሪያ ስራው የሆነው ይህ የግጥም መድበል፤ ህይወትን የሚያስውቡና በብዙ የህይወት ጉዳዮች የሚያጠነጥኑ ግጥሞች ስለተካተቱበት “የህይወት ኮስሞቲክስ” የሚል ርዕስ እንደሰጠው ጠቁሟል፡፡ መፅሀፉ በ25 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን የሚማርበት ዩኒቨርስቲ ስፖንሰር እንዳደረገው ገጣሚው ተናግሯል፡፡

Read 2710 times