66 አጫጭር ግጥሞችን ያካተተውና በተማሪ ማንያዘዋል እሸቱ የተፃፈው “የህይወት ኮስሞቲክስ” የግጥም መድበል ሰሞኑን ለንባብ በቃ፡፡
በ66 ገፆች የተቀነበበው የግጥም መድበሉ፤ ተማሪው ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ ያሰባሰባቸው ግጥሞች የተካተቱበት ሲሆን በማህበራዊ፣ በፍቅር፣ በአገር፣ በወጣትነት፣ በካምፓስ ህይወትና ሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥን እንደሆነ ታውቋል፡፡
በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርስቲ የሁለተኛ አመት የኢንቫይሮንሜንታል ኢንጂነሪንግ ተማሪ የሆነው ገጣሚው፤ የፊልም ስክሪፕት የመፃፍ ስራ ላይ ማተኮሩን ገልፆ የመጀመሪያ ስራው የሆነው ይህ የግጥም መድበል፤ ህይወትን የሚያስውቡና በብዙ የህይወት ጉዳዮች የሚያጠነጥኑ ግጥሞች ስለተካተቱበት “የህይወት ኮስሞቲክስ” የሚል ርዕስ እንደሰጠው ጠቁሟል፡፡ መፅሀፉ በ25 ብር ለገበያ የቀረበ ሲሆን የሚማርበት ዩኒቨርስቲ ስፖንሰር እንዳደረገው ገጣሚው ተናግሯል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል