በሸንቁጥ አየለ የተጻፈው “ህቡዕ ጣት” የተሰኘ ልቦለድ መፅሀፍ ለንባብ በቃ፡፡ ሃሳቡን በማብላላት እና የወቅቱን ሁኔታ ለማገናዘብ ረዘም ያለ ጊዜ የወሰደው መፅሀፉ፤ 206 ገፆች ያሉት ሲሆን በአህጉራዊና አገራዊ ጉዳይ ላይ የሚያጠነጥን እንደሆነና በተለይም የኢትዮጵያን ውስጣዊ ልዩነት በዙሪያዋ ያሉ ጠላቶቿ እንደ መሳሪያ በመጠቀም የራሳቸውን አላማ ሊያሳኩ የሚታትሩበትን ሁኔታ ያስቃኛል ተብሏል፡፡ በ45 ብር ለገበያ የቀረበው መፅሀፉ፤ የደራሲው ሁለተኛ ሥራ ሲሆን ከዚህ ቀደም “የተስፋ ክንፍ” የተሰኘ መፅሐፍ እና መቼቱን ባህርዳር ያደረገ “ማዕበል” የተሰኘ ፊልም በመፃፍና በመተወን ለእይታ አብቅቷል፡፡