Saturday, 22 March 2014 13:01

የደራሲ ለማ ደገፋ አራት መፃሕፍት ዛሬ ይመረቃሉ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

በደራሲ ለማ ደገፋ የተፃፉት “ከመሩ አይቀር”፣ “ካደጉ አይቀር”፣ “ጂሩፍ ጂሬኛ” እና “የህይወት ውቅር” መፃሕፍት ዛሬ ረፋድ ላይ በኢሊሊ ኢንተርናሽናል ሆቴል እንደሚመረቁ የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር አስታወቀ፡፡ “ካደጉ አይቀር” የተሰኘው ባለ 220 ገፅ መጽሐፍ የሰውን አዕምሮ በማልማት የሚገኝ ትሩፋት ላይ የሚያተኩር ሲሆን “ከመሩ አይቀር” የአመራርን ምንነት፣ የመሪን ማንነትና የመሪ ተግባራትን በማንሳት ትንታኔ ይሰጣል ተብሏል፡፡ መጽሀፉ 145 ገፆች እንዳሉትም ታውቋል፡፡ “የህይወት ውቅር” የተሰኘው የለማ ደገፋ ሶስተኛ ተመራቂ መጽሐፍ፤ 316 ገፆች ያሉት ሲሆን ስለመንፈሳዊ ህይወት የሚገደው የትኛውም ሰው የሚማርበትና መጽሐፍ ቅዱስን መሰረት በማድረግ የተሰናዳ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ “ጂሩፍ ጂሬኛ” የተሰኘው መጽሐፍ 367 ገፆች እንዳሉትም የኢትዮጵያ ደራሲያን ማህበር በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡

Read 2144 times