Monday, 31 March 2014 10:48

“በጎ ፈቃደኝነት” የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ሊካሄድ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

          ለችግር የተጋለጡ ህፃናትን እና በለጋ እድሜያቸው ተደፍረው ወይም ተገደው የልጅ እናት የሆኑ ሴቶችን ለመርዳትና የተሻለ ህይወት እንዲኖራቸው ለማድረግ ታስቦ ከሁለት ዓመታት በፊት የተቋቋመው መሠረት የበጎ አድራጎት ድርጅት በድርጅቱ የበጎ ፍቃድ አገልጋዮች ተነሳሽነት “በጎ ፍቃደኝነት” የሚል መሪ ቃል ያነገበ ልዩ ገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ሊያካሂድ ነው፡፡
መጋቢት 21/2006 ዓ.ም በሐርመኒ ሆቴል በሚካሄደው በዚሁ የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ ከፍተኛ የመንግሥት ባለስልጣናት፣ ባለሀብቶች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የድርጅቱ ድጋፍ ሰጪ አካላትና ሌሎች የድርጅቱ አጋሮች እንደሚገኙበት አዘጋጆቹ ተናግረዋል፡፡
“እኛው ለእኛው በእኛው” በሚል መሪ ቃል እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ የሚገኘው ይኸው ድርጅት ምንም አይነት ቋሚ የገቢ ምንጭ ሳይኖረው ጠንካራ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ የሚገኝ ሲሆን በአሁኑ ወቅት 280 ህፃናትንና 125 ሴቶችን በመርዳት ላይ የሚገኝ ድርጅት እንደሆነም ተገልጿል፡፡ ህብረተሰቡ የህፃናቱን እና የሴቶችን ህይወት ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ በሚደረገው እንቅስቃሴ ያለውን በመለገስ ሃላፊነቱን እንዲወጣ የድርጅቱ መስራች እና ዳይሬክተር ወ/ሮ መሰረት አዛገ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡

Read 1576 times