በአምስት ኢትዮጵያውያን አርቲስቶች የተቋቋመው “5 አርት ስቱዲዮና የሥዕል ጋለሪ” የፊታችን ሰኞ ተመርቆ ሥራ እንደሚጀምር ተገለፀ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በክብር እንግድነት በመገኘት እንደሚመርቁት የሚጠበቀውን ጋለሪና ስቱዲዮ ያቋቋሙት አምስት ሠዐሊዎች ሲሆኑ ተክለማርያም ዘውዴ፣ አክሊሉ ተመስገን፣ አትክልት አሰፋ፣ ዘኪሮስ ተክለሃይማኖት እና ዲሜጥሮስ ኪዳኔ ናቸው፡፡ 50 ያህል ሥዕሎችን በማሳየት ሥራ የሚጀምረው ስቱዲዮና ጋለሪ አመታዊ ፌስቲቫልና የሌሎች ሠዐሊዎችን ሥራ ለማሳየት ዝግጅት እንዳጠናቀቀ ማወቅ ተችሏል፡፡