Print this page
Monday, 31 March 2014 11:31

“ሌንሶች ለአፍሪካ ህዳሴ” የፊልም ፌስቲቫል እየተካሄደ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    ከለርስ ኦፍ ዘ ናይል ዓለም አቀፍ ፊልም ፌስቲቫል ባለፈው ሰኞ በብሄራዊ ቲያትር ለሁለተኛ ጊዜ የተከፈተ ሲሆን በዘንድሮ ፌስቲቫል ‹‹ሌንሶች ለአፍሪካ ህዳሴ›› በሚል መሪ ቃል ከመጋቢት 15- 22 የፊልም ስክሪኒግ እና ወርክሾፖች እንደሚካሄዱ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ብሉ ናይል የፊልምና ቴሌቭዥን አካዳሚ ከኢትዮጵያ የፊልም ሰሪዎች ማህበር ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ፌስቲቫል  የአፍሪካ ህብረት 50ኛ ዓመት መሪ ቃልን በማስተጋባት ሲኒማ ህብረተሰቡን በማነጽ፣በማዝናናት፣አፍሪካውያንን በማቀራረብ፣አፍሪካዊ ባህልን በማዳበር እንዲሁም ለትውልድ በማስተላለፍና ዴሞክራሲያዊ ባህልን በማጎልበት ለአፍሪካ ህዳሴ አስተዋፅኦ  እንደሚያበረክት ተገልጿል፡፡
በአሊያንስ ኢትዮ ፍራንሲስ፣ በጣሊያን ካልቸር ኢንስቲትዩት እና በብሄራዊ ሙዚየም በሚደረጉ የተለያዩ ዝግጅቶች 48 የውጪና የሀገር ውስጥ ፊልሞች ለውድድር እንደሚቀርቡ የታወቀ ሲሆን ከ22 አገራት  የተውጣጡ ከ28 በላይ የፊልም ባለሞያዎች ይሳተፉበታል፡፡ ፌስቲቫሉ የፊታችን ማክሰኞ በብሄራዊ ቲያትር በሚካሄድ የመዝጊያ ፕሮግራም ይጠናቀቃል፡፡
ባለፈው ዓመት ‹‹የአፍሪካ ሲኒማ ዘመናዊ ስፍራ›› በሚል መሪ ቃል በተካሄደው የመጀመሪያው የፊልም ፌስቲቫል፤ ከ28 አገራት የተውጣጡ ከ40 በላይ ታዋቂ የፊልም ባለሙያዎች መሳተፋቸው የሚታወስ ሲሆን 56 ምርጥ የአፍሪካ ፊልሞች ተስተናግደውበታል፡፡

Read 1539 times
Administrator

Latest from Administrator