Monday, 31 March 2014 11:36

“ዶ/ር አሸብርና ሌሎችም ታሪኮች” ለገበያ ቀረበ

Written by 
Rate this item
(7 votes)

        በአዲስ ጉዳይ መጽሔትና በድረ-ገፆች ላይ የተለያዩ መጣጥፎችንና ግጥሞችን በመፃፍ የሚታወቀው አሌክስ አብርሃም ፤“ዶ/ር አሸብርና ሌሎችም ታሪኮች” በሚል ያዘጋጀው የአጫጭር ልብወለዶች መድበል ባለፈው ሳምንት ለገበያ ቀረበ፡፡ ሃያ አምስት አጫጭር ልቦለዶችንና ታሪኮችን የያዘው መድበሉ፤237 ገፆች ያሉት ሲሆን በሊትማን መጽሐፍት አከፋፋይነት በ50.65 ብር እየተሸጠ ነው፡፡  
በሌላ በኩል በብርያን ትሬሲ ተፅፎ በእስክንድርያ ስዩም የተተረጎመው “መቶ የቢዝነስና የአመራር ህጎች” የተሰኘ የንግድ ክህሎት መፅሀፍ እየተሸጠ ነው፡፡ በስምንት ምዕራፎች ተከፋፍሎ በ142 ገፆች የተቀነበበው  መፅሀፉ፤በህይወትና በስኬት ህግጋት፣ በመሪነት፣ በገንዘብና በሽያጭ ህጎች እንዲሁም በንግድ ሥራ ህጎችና መሰል ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥን ሲሆን የተሳካ የንግድ ስራን ለመጀመር፣ ለመምራትና ለማሳደግ የሚረዳ መፅሐፍ ነው ተብሏል፡፡ የእንግሊዝኛው መፅሃፍ በብዙ ሚሊዮን ቅጂዎች እንደተሸጠና የብዙዎችን የቢዝነስና የአመራር ህይወት እንደቀየረ ተጠቁሟል፡፡ ወደ አማርኛ የተተረጎመው መፅሀፉ   በ35.45 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 3200 times