Monday, 14 April 2014 09:48

“የንጉሱ ገመና” በሚል ርዕስ ስለታተመው መጽሐፍ ከኢትዮጵያ ዘውድ ምክር ቤት የተሰጠ ይፋዊ መግለጫ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ከኢትዮጵያ ዘውድ ምክር ቤት
P.O Box 320608
Alexandera, Virginia 22320 USA
Email: This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it.
Cellphone:+1(202)32982503

“የንጉሱ ገመና” በሚል ርዕስ ስለታተመው መጽሐፍ ከኢትዮጵያ ዘውድ ምክር ቤት የተሰጠ ይፋዊ መግለጫ

በአሁኑ ጊዜ በሕይወት በሌሉት አቶ ስዩም ጣሰው ተፃፈ ተብሎ የሚነገርለትና በአቶ ግርማ ለማ ለሕትመት የበቃውን “የንጉሱ ገመና/ን/ ዳሰሳ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ ያነበብኩት በአግርሞትና በኅዘን ተውጬ ነበር፡፡
መጽሐፉ የቀ.ኃ.ሥ አልባሽ የነበረ ሰውና በዚሁ ሥራው ንጉሱን ከማንኛውም የቤተመንግሰት ሠራተኞች በተሻለ ሁኔታ ሊቀርባቸው ይችላል በሚል መላ ምት ከቀ.ኃ.ሥ ስብዕና ጋር የማይዛመድ ተራ የመንደር ወሬና ስድብን የቋጠረ ዶሴ ሆኖ እንደሚፈረጅ ለአፍታም ጥርጣሬ የለንም፡፡
ከሟች አቶ ሥዩም ጣሰው በተሻለ ንጉሱን በቅርብ የሚያውቁ በሕይወት ያሉ እንደዚያን ዘመን አጠራር “የእልፍኝ አሽከሮች” መጽሐፉ ውስጥ የሰፈሩትን አሉባልታና ስድቦች “ተረት ተረት” ነው በማለት ብቻ ከመወሰን አልፈው ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ የአይን ምስክርነታቸውን ዘገባ በማቅረብ የዜግነት የውዴታ ግዴታቸውን እንዲወጡ በዚህ አጋጣሚ ወገናዊ ጥሪዬን አስተላልፋለሁ፡፡
እዚህ ላይ መታወስ የሚባለው አንዱ ቁም ነገር አለ፡፡ ይኸውም ግፈኛው የደርግ አገዛዝ ቀ.ኃ.ሥ./ን/ በመግደል ብቻ ሳይወሰን የቀ.ኃ.ሥ./ን/ ስምና ሌጋሲ በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ጥላሸት ማልበስን ሥራዬ ብሎ ተያይዞታል፡፡ ግፈኛው ሥርዓት የተገረሰሰ ቢሆንም ዘርቶ የሄደው ክፋት፤ ምቀኝነትና ስም ማጥፋት ግን ሕብረሰባችን ውስጥ ተንሰራፍቶ ስለሚገኝ የንጉሱ ገመናም የዚሁ ነፀብራቅ እንደሆነ አያጠራጥርም፡፡
ደግነቱ ግን ዛሬ የቀ.ኃ.ሥ ትክክለኛ ማንነት እውቅና ባገኙ ዓለምአቀፍ የታሪክ ፀሐፊዎች፤ የቀ.ኃ.ሥ ሕይወት ታሪክ ፀሐፊዎች (biographers) እንዲሁም የዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች ለሕትመት እየበቃ የሚገኝበት ወቅት ላይ ስለምንገኝ የኢትዮጵያ ሕዝብ የንጉሱ ገመናን ግኝቶች ውድቅ እንደሚያደርገው እምነቴ ነው፡፡
መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ለአራት አስርተ ዓመታት ለቀ.ኃ.ሥ. ወደር የሌለው ፍቅርና ከበሬታን ቸሯቸው ኖሯል፡፡ የግል ሕይወታቸውም ቢሆን ከሕብረተሰቡ የተሰወረ አልነበረም፡፡ ሰው ናቸውና ስህተት አልሰሩም አይባልም፡፡ ቁም ነገሩ የፈፀሟቸው ስህተቶች ከአስገኟቸው የሶሽዮ ኢኮኖሚክ ድሎች ጋር ሲመዛዘኑ ግን ኢምንት ሆነው ይገኛሉ፡፡ ቀ.ኃ.ሥ ፈሪህ እግዚአብሔር ያደረባቸው አገር ወዳድና ባለ ራዕይ የነበሩ መሪ መሆናቸውን ዛሬ ታሪክ እየመሰከረ ይገኛል፡፡
ለዚህም ነው አንባቢያን ለንጉሱ ገመና ጊዜያቸውንና ገንዘባቸውን እንዳይቸሩት በትህትና ላሳስብ የምፈልገው፡፡ ታሪክ ደግሞ ደጋግሞ የሚያስተምረው ቁምነገር የሰው ስም ጥላሸት በመቀባት የሚገኝ ትርፍ አለመኖሩን ነው፡፡
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ
ልዑል ኤርምያስ ሳህለሥላሴ ኃይለሥላሴ  

Read 2444 times