Monday, 14 April 2014 09:59

የቀልድ - ጥግ

Written by 
Rate this item
(7 votes)

አንድ ባለመደብር ሰውዬ ወደ ሁሉን - አዋቂ ነኝ ባይ (Know it all) ወዳጁ ጋ ሄዶ፤
“ጠዋት ጠዋት ስነሳ ጤና አይሰማኝም፡፡ የዞረ-ምድር እንዳለበት ሰው ጥውልውል ያደርገኛል” አለው።
ሁሉን አዋቂው ሰውም፤ “ማታ ስትተኛ ወተት ጠጣ” አለው፡፡
ባለመደብሩ፤ “እኔማ በየማታው ወተት ሳልጠጣ አድሬ አላውቅም”
ሁሉን አዋቂነኝ - ባዩም፤ ወዲያው እጥፍ አለና፤ “ይሄውልህ ዋናው ችግርህ እሱ ነው፡፡”
“እንዴት”
“ቆይ ላስረዳህ፡፡ አየህ ወተቱን ትጠጣና አልጋህ ላይ ትወጣለህ ከዚያ ከግራ ወደቀኝ ትገላበጣለህ። ስትገላበጥ ወተቱ አይብ ያወጣል። ደሞ ስትገላበጥ ስትናጥ አይቡ ደግሞ ቅቤ ይወጣዋል፡፡ ከዛ ቅቤው ወደ ስብነት ይለወጣል። ስቡ ደወ ስኳርነት ይለወጣል። ቀጥሎ ስኳሩ ወደ አልኮልነት ይቀየራል። ስለዚህ ጠዋት ስትነሳ የዞረ-ምድር ናላህን ያዞረዋል። ለዚህ ነው የሚያጥወለውልህ!” አለና አብራራለት፡፡
*       *       *
አንድ ባለመደብር ሰውዬ ወደ ሁሉን - አዋቂ ነኝ ባይ (Know it all) ወዳጁ ጋ ሄዶ፤
“ጠዋት ጠዋት ስነሳ ጤና አይሰማኝም፡፡ የዞረ-ድምር እንዳለበት ሰው ጥውልውል ያደርገኛል” አለው።
ሁሉን አዋቂው ሰውም፤ “ማታ ስትተኛ ወተት ጠጣ” አለው፡፡
ባለመደብሩ፤ “እኔማ በየማታው ወተት ሳልጠጣ አድሬ አላውቅም”
ሁሉን አዋቂነኝ - ባዩም፤ ወዲያው እጥፍ አለና፤ “ይሄውልህ ዋናው ችግርህ እሱ ነው፡፡”
“እንዴት”
“ቆይ ላስረዳህ፡፡ አየህ ወተቱን ትጠጣና አልጋህ ላይ ትወጣለህ ከዚያ ከግራ ወደቀኝ ትገላበጣለህ። ስትገላበጥ ወተቱ አይብ ያወጣል፡፡ ደሞ ስትገላበጥ ስትናጥ አይቡ ደግሞ ቅቤ ይወጣዋል፡፡ ከዛ ቅቤው ወደ ስብነት ይለወጣል፡፡ ስቡ ደወ ስኳርነት ይለወጣል። ቀጥሎ ስኳሩ ወደ አልኮልነት ይቀየራል። ስለዚህ ጠዋት ስትነሳ የዞረ-ምድር ናላህን ያዞረዋል። ለዚህ ነው የሚያጥወለውልህ!” አለና አብራራለት፡፡

Read 3983 times