በኢትዮጵያ ዘመናዊ የማስታወቂያ ሥራን በፈር ቀዳጅነት እንደጀመሩ በሚነገርላቸው በአቶ ውብሸት ወርቃለማሁ የህይወት ታሪክ ላይ የሚያጠነጥን ‹‹ያልመከነ ማንነት›› የተሰኘ መጽሐፍ ከትናንት በስቲያ በሒልተን ሆቴል ተመርቆ በገበያ ላይ ዋለ፡፡
በአበበ አያሌው የተዘጋጀው ይኸው መፅሐፍ ፤ የአቶ ውብሸት ወርቃለማሁን ከልጅነት እስከ ዕውቀት የህይወት እርምጃና ስኬት የሚተርክ ነው ተብሏል፡፡ በምርቃት ሥነሥርዓቱ ላይ ሚኒስትሮች፣ አምባሳደሮች፣ የጥበብ ባለሙያዎች እና የባለታሪኩ ወዳጆች ተገኝተዋል፡፡ በ205 ገፆች የተሰናዳው መፅሐፍ፤ በ94 ብር እየተሸጠ ነው፡፡
Monday, 14 April 2014 11:08
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና