Saturday, 26 April 2014 12:08

“ኤስቪፒ ቴክስታይልስ” በ11 ቢሊዮን ብር የጥጥ ክር ፋብሪካ ሊገነባ ነው

Written by 
Rate this item
(3 votes)

ለውጪ ገበያ የሚቀርበውን የጥጥ ክር ምርት በእጥፍ ያሳድጋል
ኢትዮጵያን በአለም ከታወቁት ጥቂት የጥጥ ክር አምራች አገራት አንዷ ለማድረግ ያቀደው ኤስቪፒ ቴክስታይልስ በኮምቦልቻ በ11 ቢሊዮን ብር ወጪ ዘመናዊ የጥጥ ክር ፋብሪካ ሊገነባ መሆኑን አስታወቀ፡፡
በኮምቦልቻ የሚገነባው ፋብሪካው  በቀን እስከ 272.9 ቶን የሚደርስ ምርጥ የጥጥ ክር የማምረት አቅም እንዳለው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ፋብሪካው ምርት ሲጀምር፣ አገሪቱ በአሁኑ ጊዜ ለውጭ ገበያ የምታቀርበውን ጥራቱን የጠበቀ የጥጥ ክር ምርት፣ በእጥፍ እንደሚያሳድገው የተገለፀ ሲሆን የአገሪቱን የልማት እቅድ መሰረት አድርጎ የተቀረጸው ፕሮጀክቱ፣ በአሁኑ ጊዜ ከቅድመ ዝግጅት ደረጃ አልፎ ወደ ትግበራ እንቅስቃሴ ለመሸጋገር እያኮበኮበ ነው ተብሏል፡፡
የፋብሪካው መገንባት በውጭ ንግዱ ዘርፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት ሲሆን ለበርካታ የአካባቢው ነዋሪዎች የስራ ዕድል እንደሚፈጥርና  የተለያዩ ጥቅሞችን እንደሚያስገኝ ተነግሯል፡፡
እ.ኤ.አ በ1898 ዓ.ም  የተመሰረተውና የፕሮጀክቱ ባለቤት የሆነው የህንዱ ፒቲ ግሩፕ፣ በስሩ በርካታ ኩባንያዎችን የሚያስተዳድር ሲሆን  በጨርቃ ጨርቅ፣ በፋይናንስ፣ በሸቀጣሸቀጥ፣ በሪል እስቴትና በጌጣጌጦች የንግድ  ስራዎች ላይ በመሰማራት ትርፋማ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል ተብሏል፡፡

Read 2198 times