Saturday, 26 April 2014 13:08

ልዩ የባህል ማዕከል ሊከፈት ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

የተለያዩ የኢትዮጵያ ታሪክ፣ ቅርሶችና የብሔር ብሄረሰቦችን ባህልና ትውፊት በአንድ ላይ በማሰባሰብ ለማስጎብኘት የሚያስችል ነው የተባለ የባህል ማዕከል የፊታችን ሐሙስ ሊከፈት ነው፡፡
“ብርሃን ኢትዮጵያ የባህል ማዕከል” የሚል ስያሜ የተሰጠው የባህል ማዕከል፤ ኢትዮጵያን ቀደምት ታሪኮች የሚያወሱ ቅርሶች፣ ለአገሪቱ ታሪካዊ ቦታዎች ምሳሌ የሚሆኑ ስራዎች፣ ከአፄ ቴዎድሮስ እስከ አሁን ድረስ ያሉ የአገሪቱ መሪዎች ምስሎችና አጫጭር ታሪኮችና ብሔር ብሔረሰቦች ባህላዊ ቤቶችን አካቶ የያዙ መሆኑ ታውቋል፡፡
የማዕከሉ ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሳቤላ በላይነሽ አባይ ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት፤ ማዕከሉ ህብረተሰቡ ባህሉን በአግባቡ ለማወቅና ጎጂውን ለማስቀረት፣ ጠቃሚውን ደግሞ ለመያዝ እንዲችል የሚያግዝ መሆኑን ጠቅሰው፣ ቱሪስቶች በአንድ ጊዜ ሁሉንም አካባቢዎች ለመጎብኘት እንዲችሉ እድሉን ያመቻቸ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡
በአዲስ አበባ ቄራ ቡልጋሪያ ማዞሪያ አካባቢ የተሰራው የባህል ማዕከል፣ የፊታችን ሐሙስ በይፋ ተመርቆ እንደሚከፈትም ታውቋል፡፡  

Read 2073 times