Print this page
Saturday, 26 April 2014 13:09

“የአዕምሮ አስተዳደር ሞዴል” እና “ፍቅር ምንድን ነው” ዛሬ ይመረቃሉ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

    ነዋሪነታቸውን በለንደን ባደረጉት ኢ/ር ወንድሙ ነጋሽ ተፅፈው የተዘጋጁት “የአዕምሮ አስተዳደር ሞዴል” እና “ፍቅር ምንድን ነው” መፃህፍት ዛሬ ረፋድ ላይ በብሄራዊ ቴአትር አዳራሽ ይመረቃሉ፡፡
መፃህፍቶቹ ስሜትን ስለመቆጣጠር፣ በራስ ስለመተማመን፣ በአላማ ስለመፅናት፣ ስለ ደስታና የፍቅር ያለንን ግንዛቤ የሚያሰፉ ሲሆን “ፍቅር ምንድነው?” በሚለው መፅሀፍ ውስጥ ፍቅር ምንነትና መሰል ጉዳዮች ተዳስሰውበታል፡፡ መፃህፍቱ በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ዛሬ ሲመረቁ ውይይት ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ፀሐፊው ኢንጂነር ወንድሙ ነጋሽ ላለፉት 15 ዓመታት በእንግሊዝ የጦር መርከቦችን ከአደን የመከላከል ሲስተም መሀንዲስ በመሆን ከመስራታቸውም በተጨማሪ በስነ-ልቦና ላይ የተመሰረቱ ተከታታይነት ያላቸው ጥናታዊ መፃህፍት በመፃፍ ላይ እንደሚገኙ ታውቋል፡፡

Read 4098 times
Administrator

Latest from Administrator