Saturday, 26 April 2014 13:13

አርቲስቶችን ያፈራው “ሚያዚያ 23” ት/ቤት የወርቅ ኢዮቤልዩውን እያከበረ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በርካታ የሀገሪቱን ተዋንያን መፍለቂያ የሆነው እና ፈረንሳይ ለጋሲዮን አካባቢ የሚገኘው “ሚያዚያ 23” አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተመሰረተበትን 50ኛ ዓመት እያከበረ ነው፡፡  በ1956 ዓ.ም “አስፋወሰን ካሳ” በሚል መጠሪያ ሥራ የጀመረው “ሚያዚያ 23” በመጪው ሐሙስ ከጧቱ ሦስት ሰዓት በሚከናወን ደማቅ ሥነ-ሥርአት የቀድሞ ተማሪዎቹ እና ያሁኖቹ የሀገሪቱ አንጋፋና ታዋቂ ከያንያንና ጋዜጠኞች በትምህርት ቤቱ እንደሚገኙ የተናገሩት የትምህርት ቤቱ ርእሰ መምህር አቶ ጌታቸው አዋሽ፤ እነዚሁ ከያንያን ልምድና ተሞክሮአቸውን እንዲሁም ትዝታቸውን ለአሁን ተማሪዎችና ተጋባዥ እንግዶች እንደሚያቀርቡ ጠቁመዋል፡፡ በተጨማሪም የተለያዩ ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች የሚቀርቤ ሲሆን 50ኛ ዓመቱን አስመልክቶ እየተካሄደ ያለው የእግር ኳስ ውድድርም ይጠናቀቃል፡፡ ሥራ ሲጀምር ከ120 በታች ተማሪዎች የነበሩት ትምህርት ቤቱ፤ አሁን 1560 ያሕል ተማሪዎች ያሉት ሲሆን ከቀድሞ ተማሪዎቹ መካከል አርቲስት ጥላሁን ዘውገ፣ ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ፣ የቶክሾው አቅራቢው ሰለሞን ሹምዬ፣ አርቲስት ግርማ ተፈራ፣ አርቲስት አለልኝ መኳንንት እና ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የኤፍኤም ጣቢያዎች ዳይሬክተር የነበረው ጋዜጠኛ ሳሙዔል እንዳለ ይገኙበታል፡፡

Read 3269 times