Saturday, 26 April 2014 13:15

“ጉራማይሌ የስነ ጥበብ ማዕከል” ተመረቀ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

የስነ ጥበብ ስራዎችን ለህብረተሰቡ በማቅረብ አማራጭ መድረክ የመፍጠርና ለጥበብ አፍቃሪያን በተለያዩ አጋጣሚዎችና ስፍራዎች የስነ ጥበብ ስራዎችን የመመልከት፣ የማድነቅና ቁምነገር የመቅሰም ዕድል የመፍጠር አላማ ይዞ የተቋቋመው ጉራማይሌ የስነ ጥበብ ማዕከል፣ ትናንት ምሽት ተመርቆ ተከፈተ፡፡
የማዕከሉ መስራችና ዳይሬክተር አቶ ሚፍታ ዘለቀ እንደተናገሩት፤ ጉራማይሌ የስነ ጥበብ ማዕከል፣ ስነጥበባዊ ዋጋው ከፍ ያለ ማህበረሰብ የመፍጠር፣ የስነ ጥበቡን ማህበረሰብ ከሰፊው ህብረተሰብ ጋር የማቀራረብ፣ ስነ ጥበብን መሰረት ያደረገ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንዲሁም መንፈሳዊ ብልጽግናን የመፍጠር ግብ ይዞ ነው የተቋቋመው፡፡
ትናንት ምሽት በተከናወነው የማዕከሉ የምረቃ ስነ ስርዓት ላይ፤ ታደሰ መስፍን፣ ደረጀ ደምሴ፣ ዘላለም ግዛው፣ ዳዊት አድነውና ሌሎች አንጋፋና ወጣት ሰኣሊያን የተሳተፉበት “ጉራማይሌ - አንድ” የተሰኘ የስዕል ትርዒት ለእይታ በቅቷል፡፡

Read 2122 times