Saturday, 03 May 2014 13:13

3ተኛው ዝክረ አድዋ የኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል ሰኞ ይቀርባል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  የአድዋ ድልን 118ኛ ዓመት ክብረ በዓል ምክንያት በማድረግ “ዝክረ አድዋ” የኪነ-ጥበብ ፌስቲቫል የፊታችን ሰኞ ከ11፡30 ጀምሮ በብሄራዊ ቴአትር እንደሚካሄድ “ኬር ኢቨንትስ እና ኮሙዩኒኬሽን” አስታወቀ፡፡ ፌስቲቫሉ ለሶስተኛ ጊዜ የሚካሄድ ሲሆን የዘንድሮው የአድዋ ድል 118ኛ ዓመትና የሚያዚያ 27 የአርበኞች ድል 74ኛ ዓመት በጥምረት እንደሚከበር ድርጅቱ ገልጿል፡፡ “ዓለምን ያስደነቀውን የያኔዎቹ ጀግኖች አባቶቻችንንና እናቶቻችንን አኩሪ ድል በቴአትር፣ በሽለላ፣ በውዝዋዜ፣ በፊልም፣ በፎቶና በውይይት እንድንዘክረው ወስነናል” ብሏል አዘጋጁ፡፡
በፌስቲቫሉ ላይ መገኘት የሚፈልጉ ሁሉ እንዲታደሙለትም ጥሪውን አስተላልፏል ኬር ኤቨንትስ እና ኮሙዩኒኬሽን፡፡     

Read 1594 times