Saturday, 10 May 2014 11:21

ዳሽን ባንክ የአሜሪካን ኤክስፕረስ ካርድ አገልግሎት ሊጀምር ነው

Written by 
Rate this item
(1 Vote)


ዳሽን ባንክ እና የአሜሪካው ኤክስፕረስ ኔትወርክ የኤቲኤም የካርድ አገልግሎት ስምምነት የተፈራረሙ ሲሆን በቅርቡ የአሜሪካ ኤክስፕረስ ካርድ አገልግሎት በሁሉም የዳሽን ባንክ ኤቲኤም ማሽኖች እንደሚጀምር ተገለፀ፡፡ የባንኩ የፕሮሞሽን ዋና ክፍል ኃላፊ አቶ እስጢፋኖስ በፈቃዱ፤ የኤቲኤም ማሽን የካርድ አገልግሎቶችን እየተገበረ መሆኑን አስታውሰው፤ በሃገሪቱ ብቸኛ ባንክ የሚያደርገው፤ የአሜሪካን ኤክስፕረስ ካርድ አገልግሎት፣ የሙከራ ሂደቱ እንደተጠናቀቀ በይፋ ይጀምራል ብለዋል፡ በርካታ የውጭ ሃገር ቱሪስቶች የአሜሪካን ኤክስፕረስ ካርድ ተጠቃሚ ናቸው ያሉት ኃላፊው እስከዛሬ በዚህ ካርድ በኢትዮጵያ ውስጥ ገንዘብ ማውጣት እንደማይቻል ጠቁመው፤ ዳሽን ባንክ አገልግሎቱን መጀመሩ ብቸኛው እንደሚያደርገው ተናግረዋል፡፡ የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ ብርሃኑ ወ/ስላሴ በስምምነት ፊርማው ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ባንካቸው በኢትዮጵያ ያለውን የልማት እንቅስቃሴ እየደገፉ መሆኑን ጠቅሰው፤ እስካሁን ካሉት የኤቲኤም ካርዶች በተጨማሪ፣ የአሜሪካን ኤክስፕረስ ካርድ አገልግሎት መጀመሩ፣ ባንኩንም ሃገሪቱንም ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል ብለዋል፡፡ ዳሽን ባንክ በኢትዮጵያ ተጠቃሽ ከሆኑ የፋይናንስ ተቋማት አንዱ ነው ያሉት የአሜሪካ ኤክስፕረስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ፒተር ላይስ በበኩላቸው፤ ባንኩ ለደንበኞች አገልግሎት እርካታ የሚተጋ መሆኑን፣ የአሜሪካን ኤክስፕረስ ካርድ ተጠቃሚነቱ ይመሰክራል ብለዋል፡፡

Read 1257 times Last modified on Saturday, 10 May 2014 13:33