በፌደራል የስነምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን፣ ከባድ የሙስና ክስ የተመሠረተባቸው የቀድሞ የገቢዎችና ጉምሩክ ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ እና ምክትላቸው አቶ ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስን ጨምሮ በ3 መዝገቦች የተካተቱ ተከሣሾች ላቀረቡት የክስ መቃወሚያ ብይን ለመስጠት ፍ/ቤቱ በድጋሚ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ከትናንት በስቲያ ሐሙስ የዋለው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 15ኛ ወንጀል ችሎት፣ ተከሣሾች ያቀረቡት መቃወሚያ እና አቃቤ ህግ የሰጠው ምላሽ ተመርምሮ፣ ብይኑ ተዘጋጅቶ መጠናቀቁን አመልክቶ፣ በብይኑ ላይ የችሎቱ ዳኞች ለመወያያ አጭር ጊዜ ስለሚያስፈልጋቸው ተለዋጭ ቀጠሮ ለመስጠት መገደዱን አስታውቋል፡፡ በ3ቱም መዝገቦች ላይ ብይን ለመስጠትም ለግንቦት 8 ቀን 2006 ዓ.ም ለ3ኛ ጊዜ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡