Saturday, 10 May 2014 12:27

የአሜሪካና የቻይና የጦር መሣሪያ አራምባና ቆቦ ነው

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ተራ ሰዎች የታጠቁትን መሣሪያ ለማነፃፀር እንጂ፣ ሁለቱ መንግስታት የታጠቁትን  ለመቁጠር አይደለም። በአሜሪካ

መሣሪያ የታጠቀ ቤተሰብ ነው የሚበዛው - 58 በመቶ ያህል ቤተሰቦች የመሣሪያ ባለቤት ናቸው። ብዙዎቹም፣ ሦስት እና

አራት የመሣሪያ አይነቶች አሏቸው። የተለመደ ባሕል ወይም እምነት ብቻ አይደለም። የመሣሪያ ባለቤትነት ትልቅ ዋጋ

የተሰጠው መሰረታዊ መብት ከመሆኑ የተነሳ፤ ከ230 ዓመት በፊት የአገሪቱ ሕገመንግስት ሲፀድቅ በማይደፈሩ መብቶች

ዝርዝር ውስጥ እንዲገባ ተደርጓል። ዛሬ፣ በሲቪል አሜሪካዊያን እጅ ውስጥ ያለ የጦር መሣሪያ፣ ከ300 ሚሊዮን በላይ

ነው።
በቻይና፣ የጦር መሣሪያ ባለቤትነት፣ የሚያስቀጣ ወንጀል እንጂ የሚከበር መብት አይደለም። የጦር መሳሪያ ፈልጎ

ማግኘት ያስቸግራል። በሌላው አካባቢ ይቅርና፣ የተቃውሞና የአመፅ አዝማሚያ ይታይበታል በሚባለው ጊዝሆ በተሰኘ

የቻይና ክልልም የጦር መሳሪያ ብርቅ ነው።
በቅርቡ በክልሉ በተካሄደ ሰፊ አሰሳ ግን ብዙ ሕገወጥ መሣሪያ ተገኝቶ ተወርሷል - 12ሺ ሕገወጥ ቢላዋ።

Read 3411 times