Monday, 19 May 2014 08:51

የ5ቱ የአውሮፓ ሊጐች አጨራረስ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

ላሊጋ ነገ በኑካምፕ ይወሰናል ፤ ለአውሮፓ ሁለት ትልቅ ዋንጫዎች 3 ክለቦች እድል አላቸው
በፉክክር ደረጃው የስፔን ላሊጋ ከአምስቱ የአውሮፓ ሊጎች የላቀ ሆኗል፡፡ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የዋንጫ ጨዋታ ሁለቱ የማድሪድ ከተማ ክለቦች መገናኘታቸው፤ በዩሮፓ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ከፖርቱጋሉ ክለብ ቤነፊካ ጋርደግሞ ሌላው የስፔን ክለብ ሲቪያ መገናኘቱ የላሊጋውን ክለቦች አህጉራዊ የበላይነት ያመለክታል፡፡ ዛሬ እና ነገ የሚደረጉት የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታዎች ላሊጋውን ማን እንደሚያሸንፍ ብቻ ሳይሆን  ወራጆችንም የሚለዩ ሆነዋል፡፡ ይህ ዓይነቱ የላሊጋ ትንቅንቅ በታሪክ ለ3ኛ ጊዜ ያጋጠመ ነው ተብሏል፡፡
ከሳምንት በፊት አትሌቲክስ ማድሪድ በሜዳው ከማላጋ ጋር 1ለ1 ከተለያየ በኋላ ዋንጫውን የማያነሳበት ዕድል ተበላሽቶበታል፡፡ በሌላ በኩል በሴልታቪጐ ከሜዳው ውጭ 2ለ0 ሽንፈት የገጠመው ሪያል ማድሪድ ከዋንጫ ፉክክር ውጭ ሆኗል፡፡ እነዚህ ሁለት ውጤቶች ደግሞ የባርሴሎናን የሻምፒዮንነት ዕድል ፈጥረዋል፡፡ ስለሆነም በነገው ዕለት በካምፕ ባርሴሎና ከአትሌቲኮ ማድሪድ የሚያደርጉት ግጥሚያ ሻምፒዮኑን ክለብ ይወስናል፡፡ አትሌቲኮ ማድሪድ በ89 ነጥብና በ51 የግብ ክፍያ ሊጉን ሲመራ ባርሴሎና በ86 ነጥብና በ67 የግብ ክፍያ 2ኛ ነው፡፡
ለአትሌቲኮ ማድሪድ በነገው ጨዋታ ማሸነፍ ወሳኝ ነው፡፡  በማንኛውም ውጤት አቻ ከወጣም በ1 ነጥብ ልዩነት ዋንጫውን ከባርሴሎና ሜዳ  ይወስዳል፡፡ ይሁንና ባርሴሎና በሜዳው የሚያደርገውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ የአሸናፊው እድል በህገ ደንቦች ምላሽ ያገኛል፡፡ በላሊጋው እኩል ነጥብ የሚዳኘው ሁለቱ ክለቦችበእርስ በራስ ግንኙነት ያላቸው ውጤት ተወዳድሮ ነው፡፡ በግብ ብልጫ አሸናፊው ቢለይ እድሉ ያለጥርጥር ለባርሴሎና ነው፡፡
በሌላ በኩል በመውረድ አደጋ ውስጥ ያሉ አራት ክለቦች በመጨረሻ ሳምንት ጨወታዎች ከፍተኛ ትንቅንቅ ውስጥ ይገባሉ፡፡ በዚህ መሠረት ቫልዶሊድ ከግራንግዳ፣ ኦሳሱ መወርዱን ካወቀው ሪያል ቤቲስ ጋር የሚኖራቸው ጨዋታዎች ይጠበቃሉ፡፡

በትርፋማው የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ሁሉም ይሸለማል፤ ሲቲና የአውሮፓ ጥያቄው
 በማንቸስተር ሲቲ ሻምፒዮንነት ከሳምንት በፊት የተጠናቀቀው  የእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ለሚወርዱ ክለቦችም ከፍተኛ ገቢ በማስገኘት ትርፋማነቱ ተረጋግጧል፡፡ በሳምንቱ አጋማሽ ላይ ዴይሊሜል ባሰራጨው ዘገባ በሊጉ ተሳታፊ የነበሩ 20 ክለቦች በየደረጃው ከሚሰጥ የገንዘብ ሽልማት፣ ከቴሌቭዥን ስርጭት መብትና በተለያዩ ንግዶች ከተገኘው 1.5 ቢሊዮን ፓውንድ እንደየድርሻቸው ተከፋፍለዋል፡፡
የውድድር ዘመኑን በሁለተኛ ደረጃ የጨረሰው ሊቨርፑል ወደዋንጫው በነበረው ግስጋሴ በቀጥታ የቴሌቭዥ ስርጭት በርካታ ጨዋታዎች ተላልፈውለት ተጨማሪ ድርሻ በመያዝ በ97.54 ሚሊዮን ፓውንድ ገቢው 1ኛ ደረጃ ወስዷል፡፡ 20ኛ ደረጃ በመያዝ ከፕሪሚዬር ሊጉ የወረደው ካርዲፍ ሲቲ 62 ሚሊዮን ፓውንድ ማስገባቱ የውድድርዘመኑን ትርፋማነት አረጋግጧል፡፡
ሻምፒዮን ለመሆን የበቃው ማንቸስተር ሲቲ  በገቢ ድርሻ ሁለተኛ የሆነው በ96.56 ሚሊየን ድርሻው ነው፡፡ ቼልሲ በ94.1፣ አርሰናል በ92.9፣ ቶትንሃም በ89.7 እንዲሁም ማን.ዩናይትድ በ89.2 ሚሊዮን ፓውንድ የገቢ ድርሻቸው በተከታታይ ደረጃ የውድድር ዘመናቸውን ጨርሰዋል፡፡
ማንችስተር ሲቲ በ3 ዓመት ጊዜውስጥ ሁለት ጊዜ ሊጉን ማሸነፉ በተለያዩ አጀንዳዎች ሲያነጋግር ቆይቷል፡፡ በተለይ ክለቡ ባለፉት ሁለት የውድድርዘመናት በተጨዋቾችየዝውውር ገበያአላግባብ በማውጣት፤ በኪሳራ ግብይት በመፈፀም እና የደሞዝ ጣራን ባለመገደብ በአውሮፓ እግር ኳስማህበር የፋይናንሳዊ የስፖርታዊ ጨዋነት ህግ ይከሰሳል መባሉ የሻምፒዮንነት ፌሽታውን ያደበዘዘ ነበር፡፡ ክለቡ በአውሮፓእግር ኳስማህበር ይከሰሳሉ ከተበሃሉ 9 ክለቦችአንዱ ከሆነ በ3 ዓመት እስከ 40 ሚሊዮን ፓውንድ ሊቀጣና የተጨዋች ስብስቡን ከ25 ወደ 21 በመቀነስ ስምንት የእንግሊዝ ተወላጅ ተጨዋቾች እንዲያሰልፍ ተወሰኖበታል ነው፡፡ በዚያላይደግሞ ከሻምፒዮንስ ሊግ እንደሚባረር መገለፁ አስደንጋጭ ነበር፡፡ በመጨረሻ ሳምንት ጨዋታዎች ሻምፒዮኑ በተለየው የዘንድሮ ፕሪሚዬር ሊግ  እንደ ማንችስተር ሲቲ የሚያዝናና ክለብ አልነበረም፡፡ በተጋጣሚዎቹ ላይ ያገባቸው 102 ጐሎች ለሪከርድ አንድ የቀራቸው ነበሩ፡፡ ቼልሲ በ2009-10 የውድድር ዘመን ያስመዘገበው የ103 ጐሎች ክብረወሰን  ነው፡፡  ፕሪሚዬር ሊጉን በ89 ነጥብና ግብ ክፍያ አሳምኖ አሸንፏል፡፡ ከተመሰረተ የ129 ዓመታት ታሪክ ያለው ማንችስተርሲቲ ለአራተኛ ጊዜ ነው ፕሪሚዬር ሊጉን ያስገበረው፡፡
ማንቸስተር ሲቲ በዩናይትድ አረብ ኢምሬቲ ሼክ መንሱር ከተያዘ ካለፈት 5 ዓመታት አልፈዋል፡፡ በእነዚህ የውድድርዘመናት ሁለት የፕሪሚዬር ሊግ ዋንጫ፤ሁለት የኤፍኤ ካፕ እና ሌሎች ሁለት ዋንጫዎችሰብስቧል፡፡ የክለቨቡ ባለሃብት በተጨዋቾች ግዢ እና በደሞዝ ክፍያ እስከ 2.5 ቢሊዮን ፓውንድአውጥተዋል፡፡ ሰቲ ሊጉን እንደተቆጣጠረ ማሰብ ይቀላል፡፡ ገና በመጀመርያ የውድድር ዘመናቸው የቺሊው አሰልጣኝ ማኑዌል ፔልግሪኒ ለክለቡ 2 ዋንጫዎችን ማስገኘታቸው አድናቆት አትርፎላቸዋል፡፡ በቀጣይ የውድድር ዘመን የሚጠበቅባቸው ሻምፒዮንስ ሊግ ይሆናል፡፡
ከካርዲፍሲቲ ጋር ከሊጉ ደህና ገቢ አፍሰው መውረዳቸውን ያረጋገጡት ካርደር ሌሎቹ ሁለት ክለቦች ኖርዊችሲቲ እና ፉልሃም  ናቸው፡፡

የጋርዲዮላ ፍልስፍና ማጠቃጨቅ ጀምሯል፤ ባየር ሙኒክ የዋንጫ ሃትሪክ ይፈልጋል
አምና የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግን ያሸነፈው ባየር ሙኒክ በግማሽፍፃሜ በሪያል ማድሪድ ተባርሮ ክብሩን ባለማስጠበቁ ጭቅጭቅ ተፈጥሯል፡፡ በአውሮፓ ሻምፒዮንስሊግ ያለፉት ሃያ ዓመታት ታሪክ የትኛውም ክለብ ባልቻለው ነገር ነው ትርምሱ፡፡ በተለይከሰሞኑ ፔፔ ጋርዲዮላ በአሰለጣጠን ፍልስፍናው ከክለቡ ቁልፍ ተጨዋቾች ጋር የተፈጠረው እሰጥ አገባ ከሻምፒዮንስ ሊጉ ሽንፈት የተገናኘ ነው፡፡
በአውሮፓ ሻምፒዮንነቱ በዓለም ክለቦችዋንጫ የመጀመርያ ድሉን የጀመረው ባየር ሙኒክ ቦንደስሊጋውን እንዳሸነፈ ያረጋገጠው ከወር በፊት ነው፡፡ በአገር ውስጥ ውድድሮች ዓመቱን ለሦስት ዋንጫዎች ለመደመደም አነጣጥሯል፡፡ ከቅርብ ተቀናቃኙ ቦርስያ ዶርትመንድጋር ወሳኝ ፍልሚያ ይቀረዋል፡፡ ባየር ሙኒክ የዘንድሮ የቦንደስ ሊጋ ዋንጫ ድል በተሳትፎ ታሪኩ 24ኛው ነው፡፡

ሴሪኤ የቲቪ ገቢው ይጨምራል፤ ጁቬስ ወደአውሮፓ ይመለሳል
የጣልያኑ ሴሪኤ የሚያበቃው ነገ ነው፡፡ ጁቬንትስ የስኩዴቶውን ክብር መጐናፀፍ የቻለው ግን ከሳምንት በፊት ነው፡፡ በክለቡ ታሪክ ለ30ኛ ጊዜ  ነው፡፡ የሊጉ የመጨረሻዎቹ ሳምንት ጨዋታዎች ወሳኝነታቸው በወራጅ ቀጠና ውስጥ ባሉ ክለቦች ነው፡፡ ጁቬንትስ የስኩዴቶውን ክብር በፍፁም የበላይነት ያገኘው በሪኮርዶች በመታጀብ ነው፡፡ በሴሪኤው የመጨረሻ ሳምንት ጨዋታሌላሪኮርድ ያነጣጥራል፡፡ ከካልጋሪ ጋር በሚኖረው ግጥሚያ ሙሉ ነጥብ ከወሰደ የውድደር ዘመኑን በ102 ነጥቦች በማጠናቀቅ አዲስ ክብረወሰን ያስመዘግባል፡፡ ሌሎቹ ሪከርዶች በ25 ጨዋታዎችአለመሸነፉ እና  ለ3ኛ ተከታታይ ዓመት ዋንጫውን በመውሰድከ ዓመት በፊት የነበረውን ክብር መመለሱ ነው፡፡
በሌላ በኩል ተቀማጭነቱን በስዊዘርላንድ ያደረገው ኢንፍሮንት የተባለ ኩባንያ ሴሪኤውን በቲቪ ገቢ ለማጠናከር መወሰኑ ታውቋል፡፡ ኩባንያው በሚቀጥሉት 6 የውድድር ዘመናት የሴሪኤውን የቴሌቭዥን ስርጭት መብት ለመግዛት 4.95 ቢሊዮን ፓውንድ መክፈሉ ታውቋል፡፡ ይህደግሞ የጣሊያን ክለቦችን የገቢ አቅምበማሳደግ የትልልቅ ተጨዋቾችን ትኩረት የሚያስገኝ ይሆናል፡
ዓለም ዋንጫ ያመለጠው ኢብራሞቪችና ፒ ኤስ ጂ
በፈረንሳይ ሊግ 1 ፓሪስ ሴንት ዠርመን ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋገጠው ከሳምንት በፊት ነው፡፡ በክለቡ የ54 ዓመታት  4ኛው ነው፡፡
ለክለቡ ውጤታማነት ዓለም ዋንጫና የወርቅ ኳስ ሽልማት ያመለጠው እየተባለ የሚነሳው ስዊድናዊ ዝላታን ኢብራሞቪች ነው፡፡ ግዙፉአጥቂ ወደዓለም ዋንጫው መሄድ ባይሳካለትም በአውሮፓደረጃ ምርጥ ከሚባሉ አጥቂዎችተርታ ሆኖ አሳልፏል፡፡ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ስምንት ጎሎች ያስመዘገበ ሲሆን በሊግ1 ደግሞ በ25 ጐሎች ኮከብ ግብ አግቢ ሆኖ ጨርሷል፡፡ በፈረንሳይ ሊግ የዓመቱ  ኮከብ ተጫዋች ተብሎ ለ2ኛ ተከታይ ዓመት ተሸልሟል፡፡
በገቢ እና ወጪ ሊግ
በዋጋ ግምት
ሪያል ማድሪድ -3.44 ቢሊዮን ዶላር
ባርሴሎና - 3.28
ማን.ዩናይትድ - 2.81
ባየር ሙኒክ - 1.85
አርሰናል - 1.33
ቼልሲ - 868
ማን ሲቲ - 863
ኤሲሚላን - 856
ጁቬንትስ -850
ሊቨርፑል - 691
በገቢ (በሚሊዮን ዩሮ)
ሪያል ማድሪድ - 578.9
ባርሴሎና - 482.6
ማን.ዩናይትድ - 423.8
ባየር ሙኒክ - 431.2
አርሰናል - 284.3
ቼልሲ - 303.4
ማን ሲቲ - 863
ኤሲሚላን - 856
ጁቬንትስ -272.54
ኤሲሚላን -263.5

Read 3637 times