Saturday, 24 May 2014 15:06

የኢትዮጵያ ሙዚየም ማውጫ ታትሞ ወጣ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

“የኢትዮጵያ ህያው ሙዚየም” የተሰኘ የሙዚየም ማውጫ ታትሞ ወጣ፡፡ በሀገሬ ሚዲያ ኮሙዩኒኬሽን የተዘጋጀው ይሄው የሙዚየም ማውጫ፤ በሁለት ከተማ አስተዳደሮችና በሌሎችም ክልሎች የሚገኙ ሙዚየሞችን ይዟል፡፡ 80 ገፆች ያሉት ማውጫው፤ በክፍል አንድ ከያዛቸው ሙዚየሞች ውስጥ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚየም፣ የኢትዮጵያ ፖስታ ሙዚየም የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ሙዚየም፤ በኦሮሚያ የሻሼ ሀውልትና ባህል ሙዚየም፣ በደቡብ ክልል የስልጤ ዞን ሙዚየም፣ የሆሌሎጂ ሙዚየም፣ የኮንሶ ሙዚየምና በተለያዩ ክልሎች ያሉ በርካታ ሙዚየሞችን አካትቷል፡፡ ሀገሬ ሚዲያና ኮሙዩኒኬሽን ከዚህ ቀደም የቱሪዝም ማውጫዎችን ያሳተመ ሲሆን በቱሪዝም ላይ ትኩረት አድርጐ የሚሰራ ድርጅት ነው፡፡

Read 1976 times