የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን (ሉሲዎቹ) በኢኳቶሪያል ጊኒ አስተናጋጅነት በ2007 ዓ.ም. ለሚከናወነው 9ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ጥቋቁሮቹን ንግስቶች ከተባሉት የጋና አቻቸው በደርሶ መልስ ይፋለማሉ፡፡ የመጀመርያው ጨዋታ ነገ በአዲስ አበባ ስታድዬም የሚደረገው ነው፡፡ ሉሲዎቹ በዚሁ ፍልሚያ በሰፊ የግብ ልዩነት ማሸነፍ ከቻሉ የማለፍ እድላቸውን ያጠናክራሉ፡፡ ሁለት የወዳጅነት ጨዋታዎችን ከካሜሮንና ከናሚቢያ ብሔራዊ ቡድኖች ጋር የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በሜዳቸው እና ከሜዳ ውጭ አድርገዋል፡፡ በጥሩ ደረጃ አቋማቸውን በመፈተሽም አስተማማኝ ብቃት ላይ ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ከፕሪምየር ሊግ 12 ክለቦች የተወጣጡና 16 አዳዲስ ተጨዋቾች በሚገኙበት ቡድን በአጠቃላይ 37 ተጨዋቾች አሰባስቦ ቢያንስ ለወር ያህል ጠንካራ ዝግጅት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡
Published in
ስፖርት አድማስ